ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Wednesday, July 31, 2013

''እያበበ'' ነው የተባለው ዲሞክራሲ ለእዚች ትንሽ ጥያቄ ካልሰራ የት ይሆን የሚሰራው?




አቶ መለስ ካረፉ አንደኛ አመታቸው አልፏል።አንዳንዶች ቀለል አድርገው ለማየት ይሞክራሉ።ጉዳዩ ግን የዲሞክራሲ መታፈንን ደረጃ የሚያሳይ ነው። ለእኔ ግን የብዙ ነገር አመላካች ነው።ከአንድ አመት በኃላም እንዳስገረመኝ አለ። አቶ መለስ-
 እንዴት እንደሞቱ?

በምን ህመም እንደሞቱ?

የህመሙ ምክንያት ምን እንደነበር?
የት ሆስፒታል እንደሞቱ?

የት ሀገር እንደሞቱ?

እስካሁኗ ደቂቃ ድረስ የሀገራችን ቴሌቭዥንም ሆነ መንግስት አልነገረንም።

 በድፍኑ ''በውጭ ሀገር በህክምና ሲረዱ ቆይተው'' ከመባል ውጭ። ይህንን የመጠየቅ መብት እንዳላቸው በቅጡ የተገነዘቡ ቁጥራቸው ስንት ደርሶ ይሆን? 
አንድ የውጭ ዜጋ  ''መሪያችሁ በምን ህመም እንደታመመ፣የት እንደታከመ ሌላው ቀርቶ አስከሬን ከየት ሀገር እንደገባ ያልተነገራችሁ...ምስኪን ጭቁን ህዝቦች፣የህወሓት አባላት፣የኦህዴድ አባላት፣የብአዴን አባላት ሆይ!  እስኪ መልሱልኝ? '' ብሎ  ቢጠይቅ መልስ ያለው አለ? ይህ የሚያመላክተን አንድ እና አንድ ነገር ብቻ ነው። ይሄውም  የነፃነታችንን እና የመብታችንን ባዶነትን ነው የሚያሳየው። ''እያበበ'' ነው የተባለው ዲሞክራሲ ለእዚች ትንሽ ጥያቄ ካልሰራ የት ይሆን የሚሰራው?

ጌታቸው
ኦስሎ  

Monday, July 22, 2013

ከአምባሳደር፣ጋዜጠኛ እና ደራሲ ዘውዴ ረታ ጋር ቃለመጠይቅ (ቪድዮ)

ዛሬ ሐምሌ 15፣2005 ዓም የሲ ኤን ኤን እና ቢቢሲ ቴሌቪዥን ጣቢያዎች ትልቅ ዜናቸው ሆኖ የዋለው የእንግሊዝ ልዑላውያን ቤተሰብ  ልጅ መውለዳቸው ነበር።በማግስቱ ሐምሌ 16 ቀን ደግሞ የቀዳማዊ አፄ ሃይለስላሴ የልደት በዓል በተለይ በጀማይካውያን ዘንድ ኢትዮጵያ እና ጀማይካ ውስጥ ይከበራል።
አምባሳደር፣ጋዜጠኛ እና ደራሲ ዘውዴ ረታ ''የኤርትራ ጉዳይ'' የተሰኘውን ትልቅ ጥራዝ መፅሐፍ ጨምሮ ሌሎችንም መፃህፍት በመፃፍ ይታወቃሉ። የኢሳት ጋዜጠኛ ደረጀ ደስታ ትህትና በተላበሰ ጥያቄው አምባሳደርን አናግሯል።
አምባሳደር፣ጋዜጠኛ እና ደራሲ ዘውዴ ረታ ባለፉት ኩነቶች ላይ ሲፅፉ ምርመራዊ (investigation) መንገድን መከተላቸው የፅሁፎቻቸው ልዩ መታወቅያዎች ናቸው።
በሁለት ክፍል የተከፈሉትን ቃለ መጠይቆችን ቪድዮ ይመልከቱ።

ክፍል 1
ምንጭ - ኢሳት ቴሌቭዥን



ክፍል 2
ምንጭ - ኢሳት ቴሌቭዥን







Tuesday, July 9, 2013

አምባሳደር ብርሃኑ ዲንቃ አረፉ

አምባሳደር ብርሃኑ ዲንቃ 


  • በዲፕሎማሲው አለም ከእሩብ ክፍለዘመን በላይ አገልግለዋል።  
  • በካይሮ፣በዋሽግተን፣ነውዮርክ፣ጅቡቲ የሀገራቸው አምባሳደር ሆነው ሰርተዋል፣
  • በካምቦድያ፣ደቡብ አፍሪካ፣ሱማልያ በተባበሩት መንግሥታት ወኪልነት ሰርተዋል፣
  • በደቡብ ሱዳን የዳርፉር ግጭት በአፍሪካ አንድነት ድርጅት  ስር የነበረውን ''የስልጣን መጋራት ኮሚሽንን'' እስከ ስምምነቱ ፊርማ ድረስ በሊቀመንበርነት መርተዋል፣
  • የ ቀድሞው የተ.መ.ድ. ዋና ፀሐፊ ልዩ አማካሪም ሆነው ሰርተዋል፣
  • አሁን በቅርቡ ሕይወታቸው እስካለፈበት ድረስ በኬንያ በቀድሞው የምርጫ ወቅት ተነስቶ በነበረው ግጭት ''የእውነት አፈላላጊ ኮሚሽን'' ውስጥ በቀድሞው የኬንያ ፕሬዝዳንት ኪባኪ ተሾመው  በአለምአቀፍ ኤክስፐርትነት እና የኮሚሽኑ የሪፖርት ኮሚቴ ሊቀመንበር ሆነው እያገለገሉ ነበር።

አምባሳደር ብርሃኑ ዲንቃ በኒውዮርክ በነበረባቸው የካንሰር ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ትናንት ሰኞ ሰኔ 1፣2005 ዓም ሕይወታቸው ማለፉን የኬንያ ጋዜጦች ዘግበዋል።እረፍተ ነፍስ ይስጥልን።
source- Daily Nation,July 9,2013
            - The standard Digital news, July 8,2013

Monday, July 8, 2013

የግብፅ ኦርቶዶክስ (ኮፕቲክ) ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ፕሬዝዳንት ሞርሲን ከስልጣን ለማውረድ በተቃዋሚዎች በተጠራው የተቃውሞ ሰልፍ አንፃር እንዲህ ብሎ ነበር

የግብፅ ኦርቶዶክስ ኮፕቲክ ቤተክርስቲያን  ቅዱስ ሲኖዶስ ፕሬዝዳንት ሞርሲን ከስልጣን ለማውረድ በተቃዋሚዎች  በተጠራው የተቃውሞ ሰልፍ አንፃር እንዲህ ብሎ ነበር-
''በሰኔ 30/2013 ዓም ፕሬዝዳንት ሞርሲን ለማውረድ በተጠራው የተቃውሞ ሰልፍ ላይ ምዕመናን  የመሳተፍም ሆነ ያለመሳተፍ መብታቸው የተጠበቀ ነው።'' 
አንድመቶ ሃያ ሊቃነ ጳጳሳት በአባልነት የያዘው የቤተክርስቲያኒቱ የበላይ አካል ይህንን መግለፁን ያሳወቀው  ''አህራም ኦንላይን'' የተሰኘው የድህረ- ገፅ ጋዜጣ ነበር።
ሙሉ የ ''አህራም ኦንላይን'' የተሰኘው የድህረ- ገፅ ጋዜጣ የእንግሊዝኛ ንባብ ''ጉዳያችን ጡመራ'' ላይ ያንብቡ።



Copts free to join 30 June anti-govt protests: Egypt's Coptic Church
Coptic Church's Holy Synod says Coptic Christians are free to join planned 30 June protests against President Morsi and Egypt's Muslim Brotherhood
Ahram Online , Friday 21 Jun 2013
Egyptian Copts are free to decide for themselves whether or not to take part in planned 30 June anti-government rallies, the Holy Synod of Egypt's Coptic Orthodox Church has stated.
Synod members issued the statement at a Thursday meeting, where they also announced that a new church spokesman would soon be appointed by Coptic Orthodox Pope Tawadros II.
The Holy Synod, which is comprised of 120 archbishops, represents the church's most authoritative decision-making body.
Opposition parties and groups have issued calls for mass protests on 30 June, which will mark the end of President Mohamed Morsi's first year in office, to demand Morsi's ouster and snap presidential elections.
The protest calls were initially made by the anti-Morsi 'Rebel' campaign, which on Thursday announced that it had met its target of 15 million citizens' signatures in support of its demands.
In April, Pope Tawdros criticised President Morsi for failing to protect Cairo's main Coptic Orthodox cathedral during sectarian clashes that left two dead and dozens injured.
Later the same month, the pope told Reuters that Egypt's Coptic Christians were facing increased marginalisation.
Egypt's Christian community, accounting for an estimated 10 percent of the national population of 84 million, have long complained of discrimination in the Muslim-majority countr
y

ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።