ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Wednesday, July 31, 2013

''እያበበ'' ነው የተባለው ዲሞክራሲ ለእዚች ትንሽ ጥያቄ ካልሰራ የት ይሆን የሚሰራው?




አቶ መለስ ካረፉ አንደኛ አመታቸው አልፏል።አንዳንዶች ቀለል አድርገው ለማየት ይሞክራሉ።ጉዳዩ ግን የዲሞክራሲ መታፈንን ደረጃ የሚያሳይ ነው። ለእኔ ግን የብዙ ነገር አመላካች ነው።ከአንድ አመት በኃላም እንዳስገረመኝ አለ። አቶ መለስ-
 እንዴት እንደሞቱ?

በምን ህመም እንደሞቱ?

የህመሙ ምክንያት ምን እንደነበር?
የት ሆስፒታል እንደሞቱ?

የት ሀገር እንደሞቱ?

እስካሁኗ ደቂቃ ድረስ የሀገራችን ቴሌቭዥንም ሆነ መንግስት አልነገረንም።

 በድፍኑ ''በውጭ ሀገር በህክምና ሲረዱ ቆይተው'' ከመባል ውጭ። ይህንን የመጠየቅ መብት እንዳላቸው በቅጡ የተገነዘቡ ቁጥራቸው ስንት ደርሶ ይሆን? 
አንድ የውጭ ዜጋ  ''መሪያችሁ በምን ህመም እንደታመመ፣የት እንደታከመ ሌላው ቀርቶ አስከሬን ከየት ሀገር እንደገባ ያልተነገራችሁ...ምስኪን ጭቁን ህዝቦች፣የህወሓት አባላት፣የኦህዴድ አባላት፣የብአዴን አባላት ሆይ!  እስኪ መልሱልኝ? '' ብሎ  ቢጠይቅ መልስ ያለው አለ? ይህ የሚያመላክተን አንድ እና አንድ ነገር ብቻ ነው። ይሄውም  የነፃነታችንን እና የመብታችንን ባዶነትን ነው የሚያሳየው። ''እያበበ'' ነው የተባለው ዲሞክራሲ ለእዚች ትንሽ ጥያቄ ካልሰራ የት ይሆን የሚሰራው?

ጌታቸው
ኦስሎ  

No comments:

መንግስት ከዲፕሎማሲያዊ መፋዘዝ ይውጣ! የአረብ ሊግ በአባይ ግድብ አንጻር የወሰነውን የጸብጫሪነት ተግባር በውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር የምላሽ መግለጫ ብቻ የሚበቃ ሊሆን አይገባም።መንግስት ያልሰራው ግዙፍ ስራ ኢትዮጵያን ለአደጋ እንዳያጋልጣት ያሰጋል።

የኢትዮጵያ ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ዋና መስሪያቤት መንግስት በፍጥነት ሊሰራቸው የሚገቡት አምስት ወሳኝ ዲፕሎማሲያዊ ተግባራት ========= ጉዳያችን አለርት ========= የአረብሊግ አንዱ የሚታወቅበት መለያው እንደባዶ ቆር...