Tuesday, July 9, 2013

አምባሳደር ብርሃኑ ዲንቃ አረፉ

አምባሳደር ብርሃኑ ዲንቃ 


  • በዲፕሎማሲው አለም ከእሩብ ክፍለዘመን በላይ አገልግለዋል።  
  • በካይሮ፣በዋሽግተን፣ነውዮርክ፣ጅቡቲ የሀገራቸው አምባሳደር ሆነው ሰርተዋል፣
  • በካምቦድያ፣ደቡብ አፍሪካ፣ሱማልያ በተባበሩት መንግሥታት ወኪልነት ሰርተዋል፣
  • በደቡብ ሱዳን የዳርፉር ግጭት በአፍሪካ አንድነት ድርጅት  ስር የነበረውን ''የስልጣን መጋራት ኮሚሽንን'' እስከ ስምምነቱ ፊርማ ድረስ በሊቀመንበርነት መርተዋል፣
  • የ ቀድሞው የተ.መ.ድ. ዋና ፀሐፊ ልዩ አማካሪም ሆነው ሰርተዋል፣
  • አሁን በቅርቡ ሕይወታቸው እስካለፈበት ድረስ በኬንያ በቀድሞው የምርጫ ወቅት ተነስቶ በነበረው ግጭት ''የእውነት አፈላላጊ ኮሚሽን'' ውስጥ በቀድሞው የኬንያ ፕሬዝዳንት ኪባኪ ተሾመው  በአለምአቀፍ ኤክስፐርትነት እና የኮሚሽኑ የሪፖርት ኮሚቴ ሊቀመንበር ሆነው እያገለገሉ ነበር።

አምባሳደር ብርሃኑ ዲንቃ በኒውዮርክ በነበረባቸው የካንሰር ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ትናንት ሰኞ ሰኔ 1፣2005 ዓም ሕይወታቸው ማለፉን የኬንያ ጋዜጦች ዘግበዋል።እረፍተ ነፍስ ይስጥልን።
source- Daily Nation,July 9,2013
            - The standard Digital news, July 8,2013

1 comment:

Anonymous said...

NEFS YIMAR

7ኛው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ግንቦት 24፣2018 ዓም በከፍተኛ የሕዝብ ተሳትፎ ተጠናቋል።

ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ በሰባተኛው ብሔራዊ ምርጫ ድምፅ ሲሰጡ። ስለምርጫው ዝርዝር ጉዳይ ምን ያውቃሉ? ✓ ሰባተኛው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ 42 ፓርቲዎች እና 73 የግል ተወዳዳሪዎች ለተለያዩ ምክር ቤቶች ዕጩዎች ...