ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Monday, August 29, 2022

በትግራይ ህዝብ ስም የተለመነውን እህል ከህዝቡ ነጥቆ በልቶ እያገሳ ኢትዮጵያን ለመውረር የተነሳውን ሽብርተኛው ህወሃትን ኢትዮጵያ በምን ዓይነት ቅጣት ትቅጣው?


ህወሃት በህዝቡ ስም እርዳታ ለምኖ ለህዝብ የሚሰጠው ግን የለም

  • በትግራይ ህዝብ ስም የገባውን የእርዳታ እህል ለህዝብ ሳይሰጡ በልተው የሚያገሱት እና በተለመነ እህል እየወፈሩ ያሉት እነ ጌታቸው ረዳ እና ደብረጽዮን ናቸው።

=======
ጉዳያችን 
=======

ኢትዮጵያ ማንንም በድላ አታውቅም።ለማንም አድልታ አታውቅም።እናት ያላትን ለሁሉም ሳታዳላ ሁሉንም እኩል አሳድጋለች። የኢትዮጵያ ህዝብ የሚያህል ታጋሽ ብቻ ሳይሆን የዘር ፖለቲካ በእዚህ ደረጃ ተነዝቶበት በብዙ ፈተናዎች ውስጥ ቢያልፍም ተቻችሎ ውሎ የሚያድር በሌላ ዓለም እምብዛም አይገኝም። የህወሃት የሽብር ቡድን በአማራ እና በአፋር ከህጻናት እስከ አዛውንት ሲገድል ከአንድ ሚልዮን የሚልቁ የትግራይ ተወላጆች ላይ መሃል አገር የተፈጠረ የህዝብ ለህዝብ ግጭት የለም።

የኢትዮጵያ ህዝብ ቆራጥ እና ጀግና ህዝብ እንደመሆኑ፣መንፈሳዊም ህዝብ ነው። ቀን አዘቀዘቀ ብሎ ጎረቤቱ ላይ አንዳች ክፉ ሲደረግ ዝም አይልም።የወንድሙ እና የእህቱ ጠባቂ እራሱ ጎረቤቱ ሆኖ እስከ ዘመናችን ዘልቋል። ይህ ማለት በአንዳንድ ቦታዎች ችግር አልነበሩም ማለት አይደለም።ነገር ግን እንደ ህዝብ በዘረኞች የደረሰበት ቢከፋም ሁሉን ታግሶ አሳልፎ፣አንዱ ለአንዱ መጠለያ ሆኖ ኖሯል። ወደፊትም ይኖራል።

የሽብርተኛው ህወሃት በኢትዮጵያ ላይ የሰራው ግፍ ግን ሞልቶ ከመፍሰስ አልፏል።ኢትዮጵያ ያላትን ሰጥታ በትግራይ ህዝብ ውስጥ የተደበቀውን የህወሃት ጀሌ እንደሌሎች ልጆቿል ያላትን አብልታ፣ሳትለብስ አልብሳ አሳድጋለች። ልጇ ግን ደጋግሞ ከድቷታል።ሰውነቷል ወግቷታል።መለያ ሰንደቅ ዓላማዋን አውርዶ በራሱ እራፊ ተክቷል። ከእናቱ ታሪካዊ ጠላቶች ጋር ኢትዮጵያን ለማፍረስ አሲሮባታል።ይህንን ሁሉ አድርጓት ግን ኢትዮጵያ ልጇ እርሷን ሲወጋ የአዝመራው ጊዜ ስላለፈበት ርሃብ ሲገባ የእርዳታ እህል ከውጭ ለምና ልጇን አበላች።የትግራይ ጀሌው ግን ለእርዳታ የመጣበትን መኪና ሳይቀር ከእናቱ ከኢትዮጵያ ነጥቆ የበላበትን መሶብ መልሶ እናቱን ሊወጋበት ተጋበዘ። ከእዚህ ሁሉ ግፍ በኋላየተለመነ የእርዳታ እህል በልቶ የተለመነ እህል እያገሳ ኢትዮጵያን ለመውረር የተነሳውን የእርግማን ልጅ ህወሃትን ኢትዮጵያ በምን ዓይነት ቅጣት ትቅጣው? የሚለው ወቅታዊ ጥያቄ ነው። እናት ልጇ መጀመርያ ሲረብሽ ታልፈዋለች።ሁለተኛ መጥቶ ሲበጠብጣት በምክር እና በልምጭ መለሰችው። ይህንን ሁሉ እረስቶ የእርዳታ እህል በልቶ እያገሳ በጩቤ ሊወጋት የመጣውን የእርግማን ልጅ ህወአትን ኢትዮጵያ በምን ዓይነት ቅጣት ትቅጣው?
============/////=========

Saturday, August 27, 2022

መከላከያ እንዴት እንደሚዋጋ ያውቃል! የህወሃት ዓለምአቀፍ ሁኔታዎችም ሆነ ይውጭ ደጋፊዎቹም ተቀዛቅዘውበታል። በቀጣይ የመከላከያ እና የአየር ኃይል እርምጃዎች ከመጠንከራቸው የተነሳ ማንም ማንንም ሊወቅስ የማይችልበት ደረጃ ልንደርስ እንችላለን።

የኢትዮጵያ መከላከያ ዋና መስርያ ቤት

=======
ጉዳያችን
=======
ህወሓት በያዝነው ሳምንት በሰሜን ወሎ አንጻር የከፈተው ጦርነት ባለፈው ዓመት እንዳደረገው በርካታ የሰው ማዕበል በማንደርደር በሺዎች አስከሬን ላይ እየተረማመደ የ16ኛው ክ/ዘመን ጦርነቱን ቀጥሎበታል።ከእዚህ በፊት በነበረው ውግያ ህወሃትን አጅበው የመጡ ታዳጊዎችን የኢትዮጵያ መከላከያ እየተመለከተ እንዴት እነኝህን እገድላለሁ? በሚል ብዙ ቦታዎችን እየለቀቀ በመሄድ በህዝብ ላይ ብዙ አደጋ ደርሷል።በቀደመው ወረራ የከላከያ ኃይል እንዳሁኑ የልሆነበት እና በትጥቅም ደረጃ የአማራና አፋር ክልሎች ገበሬዎች ሳይቀሩ የትጥቅ እጥረት ነበረባቸው።ይህ ሁሉ አሁን አይኖርም።ከራሱ ከህወሃት እየገፈፈ የታጠቀ የአማራ እና አፋር ክልል ገበሬ ቁጥሩ የትዬለሌ የሚባል ነው።የአማራም ሆነ የአፋር ክልል ዛሬ ያወጡት መግለጫ የአፋር መግለጫ የዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ የህወሃትን ድርጊት እንዲያወግዝ ሲጠይቅ የአማራ ክልል ህዝብ ቀጣይ የክልሉን ጥሪ እንዲጠባበቅ አሳስቧል።

ህወሃት ዓላማው ግልጽ ነው።በሰሜን ወሎ በኩል ትንሽ ከገፋ በኋላ ወደ ምዕራብ ትግራይ አቅጣጫ ለመዞር ነው።በእዚህ ጦርነት የትግራይ ወጣትን ከማስፈጀት እና ወጣቱ የትምህርት ጊዜው የመስከረም ወርን ከማሳለፍ ባለፈ አንዳች አይፈይድለትም። ይህ በእንዲህ እያለ ህወሃት ይደግፉኛል ያላቸው የምዕራብ አገሮች እንደጠበቀው ድጋፍ ሳይሰጡት ይልቁንም ከ''ፋኦ'' የሰረቀውን እህል እንዲመልስ ማሳሰብያ ሰጥቷል።የምዕራብ አገሮች ከዩክሬን ጦርነት በፊት እና በኋላ አንድ አይደሉም።ከዩክሬን ጦርነት በፊት የነበረው ኢትዮጵያን በሙሉ ዓይን የማስፈራራት ሁኔታ አሁን በርዷል።ሩስያ የጦርነቱን አድማስ ወደ ባልካን አገሮች በዋናነት ሰርብን ማዕከል አድርጋ ትገፋለች የሚለው ግምት ሰፍቷል። ስለሆነም ኢትዮጵያም የምዕራቡን ዓለም በሙሉ ዓይኗ መጣላቷ የአሜሪካን ጥቅም በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በአፍሪካ ይላትን ጥቅም አደጋ ላይ የሚጥለው በመሆኑ አሁን ከህወሃት አንጻር ያለውን ጉዳይ በጥንቃቄ ነው የሚመለከቱት። 

ህወሃትን ሌላው ኪሳራ ላይ የጣለው የራሱ የውጭ ደጋፊዎቹ የማያሸንፈው ጦርነት ውስጥ እንደገባ እየነገሩት ነው። እነኝህ ደጋፊዎቹ መንግስት የሰላም ጉዳይ ማንሳቱን እንደድል ቆጥረው በየቲክቶኩ ሲጨፍሩ የነበሩት ሁሉ ጦርነቱ ከተጀመረ በኋላ ጠፍተውበታል። ይሄውም አብዛኛው በውጭ ያለው ማኅበረሰብ ዘመዶቹ ትግራይ ውስጥ እንዴት እንዳሉ ያልሰማ ነው።በመሆኑም ከዛሬ ነገ መንግስት ስልክ ሊቀጥልና ከቤተሰብ ጋር ልነጋገር ነው እያለ ሲጓጓ ሌላ የጦርነት አዙሪት ህወሃት ከትቶት ግራ ተጋብቷል።ህወሃት የተለመዱ ሁለት የማደናገርያ መንገዶቹን አሁንም እየደገመ ነው።ይሄውም ጥቂት አደናጋሪዎች ከተሞች ውስጥ ቀድሞ በመላክ ከተማው የተያዘ አስመስሎ አደናግሮ ህዝብ ማሰደድ እና ከኋላ መሳርያ የተደገነባቸው ጀሌዎቹን በብዛት ወደፊት መግፋት ነው።ከእዚህ በተጨማሪ በየከተሞቹ የህወሃት ጀሌ ሳይመጣ መጣ ብለው የሚያወሩትን ከወዲሁ መለየት እና ለህግ ማቅረብ ላይ ህዝቡ ሊሰራበት የሚገባ ዐበይት ተግባር ነው።

በመጨረሻም የኢትዮጵያ መከላከ በሚገባ የተደራጀ እና የሚሰራውን የሚያውቅ ነው።በብዛት የተግተለተለ ጀሌ ዓይነት ውግያ የሚከተል አይደለም። በወታደራዊ ሳይንስ እንደአገር የቱ ከየት መቅደም እንዳለበት ያውቃል።ከእዚህ በፊት መቀሌን ለቆ ሲወጣ የትግራይ ህዝብ ሁኔታዎችን ይረዳል ቆይቶም የህወሃትን እኩይ ተግባር ተረድቶ በሰራዊቱ ላይ የተፈጸመውን የጥቅምት 24 ግፍ ተረድቶ ወደ ፍትሃዊ ፍርድ መጥቶ ህወሃትን ከጫንቃው ላይ ያስወግዳል በሚል ነበር።እስካሁን የታየው ጉዳይ ግን በህወሃት በግድ የመገዛትም ሆነ በውዴታ አስገዳጅ ምክንያቶች ይህ አልሆነም። ይልቁንም ለሌላ ዙር ወረራ የትግራይ ጀሌ በህወሃት መሪነት ወደ አማራ እና የአፋር ግዛቶች ጦርነት ከፍቷል።አገር ቀልባቸውን ባጡ አሸባሪዎች ዳግም የሺዎች ህይወት ሊታመስ አይችልም።በመሆኑም በቀጣይ ቀናት  የመከላከያ እና የአየር ኃይል እርምጃዎች ከመጠንከራቸው የተነሳ ማንም ማንንም ሊወቅስ የማይችልበት ደረጃ ልንደርስ እንችላለን።አገር ከሁሉ በላይ ነች።ሁሉንም ትበልጣለች። ይህ ለሰራዊቱ ከማናችንም በላይ ይገባዋል። 
===========//////=============                                                                                            

Thursday, August 18, 2022

በግሪክ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የቤተመንግስትንም ሆነ የቤተክህነትን አፋጣኝ መፍትሔዎች ይፈልጋሉ።

ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ ግሪክ ዋና ከተማ አቴንስ እጃቸውን ከፍ አድርገው ሊቀበላቸው የወጣውን ሕዝብ ሰላምታ ሲያቀርቡ
 1947 ዓም


በእዚህ ጽሑፍ ሥር የሚከተሉት ንዑስ ርዕሶች ያገኛሉ።
  • ኢትዮጵያና ግሪክ
  • የወጣቷ ኢትዮጵያዊት እናት ጭንቀት በግሪክ፣
  • በግሪክ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የችግሮቻቸው መፍትሔዎች እራሳቸው ኢትዮጵያውያኑ ጋር እና አዲስ አበባ ቤተመንግስትም ነው
  • ከቤተክህነት የሚጠበቀው አፋጣኝ መፍትሔ
==============
ጉዳያችን ልዩ ሪፖርታዥ
==============

ኢትዮጵያና ግሪክ

ኢትዮጵያና ግሪክ ወደኋላ ከአምስት ሺህ ዓመታት በላይ ታሪክ ያላቸው ጥንታውያን አገሮች ውስጥ በቀዳሚነት ከሚቀመጡት ውስጥ ናቸው።800 ዓዓ አካባቢ የኖረው የግሪክ ባለቅኔ ሆሜር ኢትዮጵያን በጽሑፉ ከትቧታል። በግሪክ አይቲዮፕያ የጠይም ሰው መገለጫ ነው። ኢትዮጵያ እና ግሪክ የጥንቱ የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን  ከፍተኛ ቁጥር ያለው ህዝብ ስላላቸው ብቻ ሳይሆን በቀላሉ የማይቦረቦር ክፍለ ዘመናትን በኩራት የተሻገረ ባሕል ባለቤቶች ናቸው።ከእዚህ በዘለለ ወደ የጥንቱ የዓለም ታሪክ ስንሄድ ኢትዮጵያ በቀይባህር ላይ ባላት የበላይነት፣ግሪክ ደግሞ በሜዴትራንያን ባህር ላይ ባላት ስልታዊ ወሳኝ አቀማመጥ አንጻር ከንግድ ግንኙነት በላይ ተጽዕኖ ፈጣሪነታቸው ጉልህ ነበር።

በዘመናዊዋ ኢትዮጵያ በቀዳማዊ  አጼ ኃይለሥላሴ ዘመን ኢትዮጵያ እና ግሪክ ግንኙነት ወደ ከፍተኛ ደረጃ የተሸጋገረበት ነበር።ንጉሱ በ1947 ዓም ግሪክ ዋና ከተማ አቴንስ ሲገቡ የአቴንስ ሕዝብ በከፍተኛ ቁጥር በአደባባይ ወጥቶ ተቀብሏቸዋል። በሁለተኛው የዓለም ጦርነት በጸረ ፋሽሽት ትግል አኩሪ ገድል የፈጸመው የግሪክ ህዝብ በአውሮፓ ደርሶ እንደነበረው ጦርነቱ እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር 1945 ዓም እንደተጠናቀቀ ረሃብ ገብቶ ነበር። በእዚህ ጊዜ ታድያ አፄ ኃይለሥላሴ አቴንስ ከተማ ተገኝተው ቁጥሩ ብዙ የሆነ የቁም ከብት ገዝተው ህዝቡን በአደባባይ ስጋ አብልተዋል። ይህ ሥጋ ህዝቡን ያበሉበት ቦታ አሁን ድረስ አቢሲንያ አደባባይ ይባላል።የእዚህ ጽሑፍ አዘጋጅም ቦታው ድረስ ሄዶ በአደባባዩ ዙርያ ያሉ ባለሱቆችን ለምን የአቢሲንያ አደባባይ ተባለ ብሎ ሲጠይቃቸው ይህንኑ ንጉሱ የሰሩት የቸርነት ሥራ አስታውሰው ነግረውታል። 

ግሪኮች በንጉሡ ጊዜ በተለይ ወደ ኢትዮጵያ እየመጡ በመኖር በንግድ፣በመምህርነት፣በግንባታ እና በተለያዩ ሙያዎች ተሰማርተው ለኢትዮጵያ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርገዋል።እዚህ ላይ የሱፐርማርኬት ባለቤቱ እና ከቤቴ የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ተለይቶኝ አያውቅም ያለው አቶ ባምቢስን ማስታወስ ይቻላል።ይህ ሁሉ ሆኖ በአሁኑ ጊዜ ግን ኢትዮጵያውያን እና ግሪካውያን ግንኙነት ላይ በጣም የጠለቀ ግንኙነት አይታይም።አዳዲሶቹ የሁለቱ አገሮች ትውልዶች በሚገባ መተዋወቅ እንዲችሉ የባሕል ልውውጥ እና የንግድ ግንኙነታቸውን ማሳደግ አለባቸው።

ዛሬ ላይ የወጣቷ ኢትዮጵያዊት እናት ጭንቀት በግሪክ

ግሪክ በሺህ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን እንደሚኖሩባት ይነገራል።ኢትዮጵያውያን ወደ ግሪክ የሚመጡት ባብዛኛው በስደተኝነት ሲሆን የሚገቡበት አቅጣጫ በሦስት መንገድ ነው። እነርሱም በቀጥታ በአይሮፕላን ከአዲስ አበባ፣በቱርክ እና በሊብያ በኩል እንዲሁም ከመካከለኛው ምሥራቅ በኩል ነው።ግሪካውያን ኢትዮጵያውያንን ይወዳሉ፣ያመሰግናሉ።ኢትዮጵያውያን ጥሩዎች እና ታማኞች ናቸው የሚለው አባባል ከታክሲ ነጂ እስከ የላይኛው የሃብት ደረጃ ያሉ ግሪካውያን ይመሰክራሉ።

የስደተኞቹን ሁኔታ ለመግለጽ የእዚህ ጽሑፍ አቅራቢ የተመለከተውን እንዳለ ማቅረቡ ለአንባቢ ስዕሉን ይሰጣል።

እድሜዋ ገና ሓያዎቹ መጀመርያ ያለች ወጣት ነች።በተደላደለ ኑሮ ላይ እንደነበረች ታስታውቃለች።ግሪክ በሆነ አጋጣሚ ስደት ብላ ከአገሯ እንደወጣች ነው የነገረችኝ።ሁለት ልጆቿን የወለደችው ግሪክ ነው። ቋሚ ሥራ እንዳትሰራ ልጆቿን የምታውልበት ያስፈልጋታል።ስለሆነም መሥራት ከሚገባት በታች ለመሥራት ተገዳለች።ከቤተክርስቲያን ወጥታ ሁለቱ ልጆቿ ቤተክርስቲያኑ በር ላይ ሲጫወቱ ፍዝዝ ብላ ታያቸዋለች።ልጆቹ የእናታቸው ሃሳብ እና ጭንቀት አይገባቸውም።እናት በግሪክ ያላት ጊዜያዊ ፈቃድ ስለሆነ ነገ የእርሷም ሆነ የልጆቿ ዕጣ ያሳስባታል። ከእዚህ ሁሉ በላይ የሚያሳዝነው ደግሞ ልጆቿ ትምሕርት መጀመር ባለባቸው ጊዜ ላይጀምሩ ይችላሉ።ምክንያቱም ፈቃድ የሌለው ወላጅ ልጆቹን ሲያስመዘግብ የሕጋዊነት ፍቃድ አብሮ ይታያል።ይህ ሁኔታ ከአንዱ ትምሕርት ቤት ወደሌላው ይለያያል።አንዳንዱ ጋር ያጠብቃሉ።ሌላው ጋር ሊላላ ይችላል። ወታቷ እናት ልጆቿ ሲጫወቱ ፈዛ የምታስበው ይህንን ሁሉ ነው።

ከእዚህ በተለየ በርካታ ኢትዮጵያውያን ሰርተው የሚኖሩ እና ከእርሳቸው አልፈው ለቤተሰብም የሚደጉሙ ናቸው።አብዛኛዎቹ የአዲሱ ትውልድ አካል የሆኑ እና ትኩስ አምራች ኃይል ናቸው።ከቤተክርስቲያን እስከ የእርስ በርስ መተሳሰባቸው፣የተቸገሩትን የመርዳት እና የመተባበር አቅማቸው እና ማኅበራዊ ኑሯቸው የሚያስደንቅ ነው።ከሥራ በኋላ ያላቸው የማኅበራዊ ኑሮ ግንኙነታቸው እና በጋራ በደስታ የመገናኘታቸው ሁኔታ ሁሉ አስደናቂ ነው።

በግሪክ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የችግሮቻቸው መፍትሔዎች እራሳቸው ኢትዮጵያውያኑ ጋር እና አዲስ አበባ ቤተመንግስትም ነው

በግሪክ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ካሉባቸው ችግሮች ውስጥ ዋና ዋናዎቹ እና መፍትሔዎቻቸው 

ችግሮቹ  
  • በሚገባ አለመደራጀት፣
  • የጋራ መገናኛ ሚድያ አለመኖር፣
  • የስደተኞቹን የፈቃድ አሰጣጥ እና በአውሮፓ ሕብረት ሕግ የተሰጣቸው መብት ለግሪክ መንግስት አቅርቦ የሚያስረዳ የሕግ ባለሙያ ማጣት፣
  • በዓለም አቀፍ ሕግ መማር የማንኛውም ሰው መብት ሆኖ ሳለ አንዳንድ ትምሕርትቤቶች ፍቃድ የሌላቸው ወላጆች ልጆች ትምሕርት ቤት ለማስመዝገብ የሚያዩት ፈተናዎች፣
  • መሰረታዊ የገንዘብ አያይዝ ስልጠና አለማግኘት።ከእዚህ ጋር ኢትዮጵያውያኑ ሰርተው የሚያገኙትን ገንዘብ ምን ዓይነት አዋጭ እና አትራፊ ነገር ላይ ማዋል እንዳለባቸው ምክር ይፈልጋሉ።
መፍትሔዎቹ 

1/የኢትዮጵያ መንግስት ክፍተኛ ልዩ ልዑክ ወደ ግሪክ ልኮ ከግሪክ መንግስት ጋር በሚከተሉት ወሳኝ ነጥቦች ላይ ከሚመለከታቸው ባለስልጣናት ጋር መነጋገር አለበት።እነርሱም 
                i / የኢትዮጵያውያን የስደተኛ ወረቀቶቻቸው ሲያድሱላቸው እንዲቀላጠፍ እና የኢትዮጵያውያንን ጉዳይ የግሪክ መንግስት በልዩ ሁኔታ እንዲታይ ታሪካዊ ግንኙነታችንን ጠቅሶ እንዲሻሻል ማስደረግ ይቻላል።የግሪክ ሕዝብ ኢትዮጵያውያንን በጣም ነው የሚረዳው።ነገር ግን በመንግስት በኩል ያሉ ቢሮክራሲዎች እንዲሻሻሉ እና ኢትዮጵያውያኖች ለግሪክ ኢኮኖሚ የሚያደርጉትን አስተዋጾ እንዲጨምር ማግባባት ይቻላል።

                ii / ፍቃድ የሌላቸው ወላጆች ልጆቻቸው በቀላሉ ትምህርት ቤት የመግባታቸው ሂደት ቢሮክራሲው እንዳያደናቅፍ የኢትዮጵያ መንግስት በግልጽ ከግሪክ መንግስት ጋር መነጋገር አለበት።ይህ ዓለም አቀፍ መብት ከመሆኑ አንጻር ኢትዮጵያም ግሪክም ትምህርት ለሁሉም አስገዳጅ ዓለም አቀፍ ሕግ ፈራሚ ናቸው።

2/ የኢትዮጵያ መንግስት ልዑካንን ልኮ ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን ማነጋገር አለበት።ልዑኩ ከኢትዮጵያውያኑ ምን ድጋፍ እንደሚፈልጉ፣ወደ አገር ቤት መመለስ የሚፈልጉ ካሉ ለመመለስ ድጋፍ የሚደረግበት መንገድ ማመላከት ያስፈልጋል።

3/ የኢትዮጵያ መንግስት ከግሪክ ጋር ያለውን የባሕል ልምድ ልውውጥ ማጠናከር አለበት።ግሪክ በባሕል የበለጸገ አገር ነች። የኢትዮጵያ የባሕል ልዑካን ወደ ግሪክ እየመጡ ግሪካውያንንም ወደ ኢትዮጵያ እየሄዱ ሁለቱ ህዝቦች የሚተዋወቁበትን መንገድ መክፈቱ ለረጅም ጊዜ በሁለቱ አገሮች ያለውን ግንኙነት ቢያጠናክርም በግሪክ ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያንም በግሪካውያን ዘንድ ባሕላቸውን እንዲያስተዋውቁ እና በኩራት እንዲሄዱ የማድረግ ፋይዳው ከፍተኛ ነው።

4/ ኢትዮጵያውያን በሚገባ መደራጀት አለባቸው። የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ በከፍተኛ ደረጃ መጠናከር ያስፈልገዋል። ለእዚህም ከአደረጃጀት እስከ ዘመኑን የዋጀ መዋቅር አሰራሮችን ማዘመን እና እያንዳንዱ ኢትዮጵያውያንን በቀላሉ በቴክኖሎጂ ተደራሽ በሆነ መልኩ የመድረስ አቅም ማስፋት ያስፈልጋል።ካልተደራጁ በቀላሉ መጠቃት ይመጣል።ኢትዮጵያውያን ከሚሰሩባቸው ቦታዎች የሚነሱ ክርክሮች፣በደሎች ቢኖሩ በቀላሉ ኮሚኒቲያቸው የሕግ ክፍል አብሯቸው እንዲቆም ማድረግ ይቻላል። 

ከቤተክህነት የሚጠበቀው አፋጣኝ መፍትሔ

በግሪክ አንዱ እና የብዙ ኢትዮጵያውያንን አዕምሮ የሚፈትነው ጉዳይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ሲንከባለሉ የመጡት ችግሮች የህዝቡን ማኅበራዊ ግንኙነት እስከማወክ መድረሳቸው እና መንግስትም ሆነ ቤተክህነት በጥብቅ ተከታትለው አፋጣኝ መፍትሔ እንዲወሰድ ማድረግ አለባቸው። በሥራ የደከመ ኢትዮጵያዊ በሰንበት ከአምላኩ የሚገናኝበት የሰላም ቦታ ይፈልጋል።የቤተክርስቲያን አንዳንድ ችግሮች ቀኖናዊ እና ስርዓታዊ በመሆናቸው ግሪክ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የሚፈቱት ሳይሆን የግድ ቤተክሕነት ጊዜ ሳይሰጥ መፍትሄ መስጠት የሚገባቸው ናቸው።በእዚህ ጉዳይ ዝርዝር ሁኔታ ላይ ጉዳያችን ወደፊት ችግሩ በቶሎ ካልተፈታ እንደ አስፈላጊነቱ በዝርዝር ትመለስበታለች።ሆኖም ግን መፍትሄው በቶሎ ከመጣ ለታሪክ መዝገብ ይቀመጣል።

በአቴንስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ከቤተክርስቲያንነቷ ጋር አብሮ የሚታየው ኢትዮጵያን በግሪክ የምትወክል ትልቅ ተቋም ነች። ትልቅ ተቋም እንድትሆን ደግሞ ከመንፈሳዊ አገልግሎቷ በተጨማሪ ለግሪካውያን ትልቅ ፋይዳ ያለው የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን አንጻር ብዙ ጉዳዮች ላይ በመሳተፍ ኢትዮጵያን የማስጠራት አቅም አላት።

በግሪክ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አንጻር ቤተክህነት ሁለት ጉዳዮች ላይ አትኩሮ መስራት አለበት

1/ የመልካም ተግባቦት ( Good Communication) ያለው አገልጋይ እንጂ የመልካም ተግባቦት ችግር ያለበት አገልጋይ ወደ ውጭ አለመላክ

የተግባቦት ክህሎት (Communication Skill) አማርኛ መናገር፣ግዕዝ መቻል ወይንም እንግሊዝኛ የማቀላጠፍ ጉዳይ አይደለም።የምዕመኑን ባሕላዊ ዕሴት፣ከተሜነት ወይንም ከገጠር የመጣ፣ከሩቅ ምስራቅ የመጣች እህት ወይንም ከአዲስ አበባ የመጣች ምዕመን ሁሉ ልዩ አቀራረብ ይፈልጋሉ።ልዩ የተግባቦት ክህሎት እና የመረዳት አቅም ይፈልጋል። እንደ ክርስቶስ ዝቅ ብሎ ለትንሽ ለትልቁ መታዘዝ እና የወጣቱንም ሆነ የአረጋውያንን ችግር ወርዶ ጠይቆ መርዳት እና አንደበትን ከክፉ አነጋገር ሁሉ ማቀብ ይፈልጋል። ህዝብ ተግባቦት ሲያጣ ተስፋ ይቆርጣል፣የሚሰጠው ክብር ይቀንስበታል።

የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን በተለይ ወደ ውጭ የምትልካቸው አገልጋዮች በውጭ ያለው ኢትዮጵያዊ ከሁሉም የአገሪቱ ክፍል ከመምጣቱ አንጻር ብቻ ሳይሆን ያለውን ነባራዊ አካባቢያዊ ሁኔታ የመተንተን አቅም እንዲኖራቸው ልዩ የተግባቦት እና ሌሎች ተጨማሪ ስልጠናዎች ቤተክርስቲያን ሰጥታ መላክ አለባት።ይህ በውጭ አገሮች ያሉ ችግሮች ሁሉ መገለጫ ነው ባይባልም አንዱ ቀላል የሚመስለን ነገር ግን ቋጥኝ የሚያህል ችግር የሚያመጣው የተግባቦት ክህሎት ማነስ ነው።

2/  የቅዱስ ሲኖዶስ አካል ከአገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ጋር ወደ ግሪክ መምጣት እና ችግሮቹን ፈትቶ የመሄዱ አስፈላጊነት 

የግሪክ የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ችግር የመልካም ተግባቦት ጉድለት ጉዳይ ብቻ አይደለም።ጳጳሳት ከአገልጋይ ካህናት ጋር በር ዘግተው ቀኖናዊ ጉዳዮችን መርምረው ውሳኔያቸውን ከቤተክርስቲያኒቱ ፍትሕ መንፈሳዊ አንጻር መርምረው ውሳኔያቸውን ለምዕመኑ ማስታወቅ አለባቸው። እዚህ ላይ የቅዱስ ሲኖዶስ ልዑክ ከአገረ ስብከቱ ጳጳስ ጋር ወይንም የአገረ ስብከቱ ጳጳስ በቤተክርስቲያን ቀኖና መሰረት የሚወስኑት ውሳኔ የመቅደሱ ጉዳይ ነው። ምዕመናን ከመቅደስ ውስጥ ስላለው አገልግሎት ስለ ማዕጠንቱ፣ስለ አቀዳደሱ ወዘተ ሃሳብ የመስጠት መብት የላቸውም።ይህ ስልጣነ ክሕነት ይጠይቃል። የቅዱስ ሲኖዶስ ልዑክ ጉዳዮቹን ለምዕመናን የማይነገሩ ካሕናት ብቻ የሚያውቋቸው ጉዳዮች ከቤተክርስቲያኒቱ ህግ አንጻር መርምረው ለሚወስኑት ውሳኔ ድንጋይ አንስቶ ይህን ካልወሰናችሁ፣ይህንን ለምን ወሰናችሁ ካለ ይህ መቅደስ ውስጥ ገብቶ ስለ ማዕጠንቱ እና ቅዳሴው ልናገር የማለት ያህል ነው።

ስለሆነም ለምን እንደተወሰኑ አደባባይ የማወጡ ጉዳዮች ላይ አባቶች በር ዘግተው ተወቃቅሰው የሚወስኑት ውሳኔ ስላለ የምዕመኑ ድርሻ አባቶቹን ተቀብሎ ውሳኔዎቹ የመቀበል እና ቤተክርስቲያኑን የማገልገል ድርሻ ነው። ይህ የቤተክርስቲያን ሥርዓት ነው።በመቅደሱ የውስጥ ጉዳይ ምዕመናን በማያውቁት ጉዳይ አይገቡም። ምዕመናን የማይረዱት ጉዳይ አባቶች ይተዛዘናሉ።የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት አባቶች ስልጣነ ክህነት አክብሮ ውሳኔዎችን አክብሮ መሄዱ ጥያቄዎች ሲኖሩ በጨዋነት ማቅረብ እንጂ በተረበሸ እና ስሜታዊ በሆነ መልኩ አባቶች ፊት መቅረብ አይገባውም። 

ያለፉት ሁሉ ትምህርት ሆነው ያልፋሉ።ለምን ሆኑ ብሎ መቆጨቱ አሁን አይጠቅምም።ለእግዚአብሔር ቤት የቀና የሚመስለው በስሜት ብዙ ነገሮች አድርጎ ይሆናል።እግዚአብሔር ልብን ስለሚመረምር ከእግዚአብሔር ቤት ቅናት አንጻር ያደረገው መሆኑን እግዚአብሔር ስለሚመረምር፣ላለፈው ንስሃ ገብቶ ለመጪው ጊዜ ቤተክርስቲያንን የበለጠ ለመካስ መነሳት ነው ቁም ነገሩ። ቅዱስ እስጢፋኖስ ሲወገር በሉት እያለ የወጋሪዎቹን ልብስ ይጠብቅ የነበረው የበፊት ስሙ ሳውል በኋላ የእግዚአብሔር ምርጥ ዕቃ የሆነው ቅዱስ ጳውሎስ ነበር። እግዚአብሔር ቅዱስ ጳውሎስ ለእግዚአብሔር እቀናለሁ ብሎ ካለማወቅ እንዳደረገው ልቡን ያውቅ ስለነበር ወደ ቀናው መንገድ መርቶ የቤተክርስቲያን ብርሓን ቅዱስ ጳውሎስ ተብሏል። ስለሆነም ያለፈው ሁሉ በስህተት የነበሩ ንግግሮች፣በጉልበት የተፈጸሙ ድርጊቶች ሁሉ ለቤተክርስቲያን ቅናት ነገር ግን በማይገባ መንገድ የተፈጸመ ቢሆንም ለእዛ ንስሃ ገብቶ ለመጪው መልካም አገልግሎት መትጋት ነው አሁን የሚያስፈልገውል።

ለማጠቃለል ግሪክ አገሩም ህዝቡም ሰው ወዳጅ ነው።በእዚህ ደግ እና ሩህሩህ ህዝብ መሃል የሚኖሩት ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ትኩረት ከመንግስት ይፈልጋሉ። ብዙ ጊዜ የኢትዮጵያውያን ስደተኞች ችግሮች ላይ የመንግስት ትኩረት ያለው ባብዛኛው በመካከለኛው ምሥራቅ ያሉት ላይ ነው።በእርግጥ በመካከለኛው ምሥራቅ ያሉ ወገኖቻችን ትኩረት ያስፈልጋል።ግሪክ ያሉ ኢትዮጵያውያንም በቀላል ዲፕሎማሲያዊ ንግግር ከግሪክ ጋር በማድረግ ብዙ ከባድ ጉዳዮች ሊፈቱ ይችላሉ።በመሆኑም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዝርዝር ጉዳዮች አጥንቶ በቶሎ መድረስ አለበት። በሌላ በኩል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ችግር የመፍታቱን ጉዳይ ቤተክህነት በኩል በቶሎ መፈጸም አለበት።እዚህ ላይ ከእዚ በፊት የተወሰኑ ውሳኔዎች አሉ ከተባለም እነርሱ ተግባራዊ እንዳይሆን የገጠሙ ችግሮች ምክንያትነት መርምሮ ማየት አስፈላጊ ነው።በግሪክ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የቤተመንግስት እና የቤተክህነት አፋጣኝ ድጋፍ ይፈልጋሉ።
=================///==========

ከእዚህ በታች ቀዳማዊ አፄ ኃይለስላሴ በ1947 ዓም አቴንስ፣ግሪክ ለጉብኝት ሲገቡ የአቴንስ ነዋሪ ያደረገላቸውን የሞቀ አቀባበል የሚያሳይ አጭር ቪድዮ ይመልከቱ።




Sunday, August 14, 2022

አለማወቅ ድንቁርናን ይወልዳል ፊደል ቆጥረናል የሚሉ ነገር ግን ከጥናታዊ ማስረጃ ይልቅ በግምት እና በቡና ላይ ወሬ የተጠመዱ በኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን የሥራ ባሕል አስተምሮ ላይ በሚነዙት አሉባልታ ትዝብት ላይ ወድቀዋል። (ከጽሑፉ መጨረሻ ማስረጃ ቪድዮ ያገኛሉ)


=======
ጉዳያችን 
=======
አለማወቅ ኃጢአት አይደለም።አለማወቅ በማወቅ ስለሚስተካከል ችግር የለውም።ባለማወቅ ውስጥ ተጀቡኖ ወደ ድንቁርና መምዘግዘግ ነው ጥፋት የሚሆነው።የኢትዮጵያ የቀደመ ዘመን ስኬቷ የሚያውቋት ምሑራን (በየዘመኑ የነበሩት ጠቢቦቿ) ስለነበሯት ነው።ምሑር፣አዋቂ፣ጥበበኛ የሚሉት ቃላት ከሆነ የአውሮፓና የአሜሪካ ዩንቨርስቲ መመረቅ ብቻ ባልሆነበት ዘመን፣የኢትዮጵያ ነገስታቷ፣የእምነት መሪዎቿ እና ጸሓፊዎቿ ሁሉ ከልጅነታቸው ታሽተው፣ተሞርደው እና ስለው የሚወጡባቸው የዕውቀት ማዕድ የሚቋደሱባቸው ሁነኛ ማዕከላት ነበሯቸው። አውሮፓ እና አሜሪካ ደርሶ የጥናት ጹሑፍ አስረክቦ ከእዛ በኋላ አንድም መጽሓፍ ሳያነቡ አልያም በተማሩት ትምሕርት የሚኖሩበትን ማኅበረሰብ ችግር ለመፍታት ምንም ሳይሞክሩ እየተቹ የሚኖርበት ዘመን አልነበረም። ኢትዮጵያ በቀደመው ዘመኗ ለነገስታትነት የሚታሰብ ወይንም የንጉሱ ልጅ በመሆኑ ንግስናው ጊዜውን ጠብቆ ይመጣል ተብሎ የሚታሰብ ልጅ በልጅነቱ ለመንፈሳዊ፣አስተዳደራዊ እና የሕግ ትምህርት ወደ ገዳማት ይላካል።ከመንፈሳዊው ጋር አቅሙ ሲጠነክር ወታደራዊ ትምህርትም አብሮ እንዲካን ከፈረስ ግልብያ እስከ ተኩስ፣አደን እና ትግል ሁሉ ይሰለጥናል። ከስር ታሽቶ፣ተሞርዶ እና ተስሎ እንጂ አሁንም በሁለት እና ሦስት ወረቀቶች ምሑር ተብሎ ጎልምሶ፣ምሑር ተብሎ እንዲያረጅ አይፈቀድለትም። እነኝህን መንፈሳዊ እና የጦር ትምሕርቶች ተምሮም በእየጊዜው ያለው ችሎታ በራሱ በህዝቡም በመኳንንቱም ከሚናገረው፣ከሚፈርደው ፍርድ፣ከሚወስነው ውሳኔ እና ከጦር ሜዳ ውሎዎቹ ሁሉ አንጻር ይለካል እንጂ አበቃ ደቀቀ የሚባል ነገር የለም።

ከ20ኛው ክ/ዘመን የመጀመርያ ሩብ ጀምሮ ግን ምሑር ማለት እንግሊዝኛ እና ፈረንሳይኛ የተናገረ፣ከአውሮፓ እና አሜሪካ ዩንቨርስቲ የወጣ፣አለባበሱ ከአገሩ ባህል ይልቅ የሸሚዝ ኮሌታው ላይ ክራቫት ያንጠለጠለ ሆኗል። ኢትዮጵያ ቀድሞ የነበሯትን አገር በቀል ዕውቀት የያዙ እየተገፉ የውጭውን የተካኑ ብቻ ቦታ አገኙ። በደራሲ ከበደ ሚካኤል  ዘመን የነበሩ የውጭ አገር መምሕራን ይህንን አስተሳሰብ እንዴት እንደሚያቀላጥፉት አንድ የዘመኑ የዐይን ምስክር ሲናገሩ። ዳግማዊ ምንሊክ ትምህርት ቤት የነበሩ የውጭ አገር መምህራን በጊዜው ከገጠር የመጣ እኛ ጋሼ የምንለው ሰው በአገሩ ሸማኔ የተሰራ ኩታ አድርጎ በመግባቱ እንዲሳቅበት አድርገው መሬት እንዲቀመጥ ሲያደርጉ እኛ ጉርድ ሸሚዝ በክራቫት ያደረግነው ወንበር ላይ እንድንቀመጥ ያደርጉን ነበር ማለታቸውን የእዚህ ጽሑፍ አዘጋጅ ያስታውሳል።

ይህ ሥር የያዘ የራስን ዝቅ አድርጎ የማሳየት ቅኝ ገዢያዊ አስተሳሰብ እየቆየ ውጭ ተምረው የመጡ ገንዘባቸው እያደረጉት መጡ።በተለይ በሚገባ በማያውቋት፣በአጥሯ ስር ደጋግመው በማለፋቸው የሚያውቋት የሚመስላቸው ወይንም አባቴ ቄስ ነበር፣እኛ ሰፈር ቤተክርስቲያን ነበር ወዘተ በሚሉ አነጋገሮች የሚታወቁ ''ምሑራን'' ነን ባዮች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን የሥራ ባሕል አስተምሮ፣መርህ እና መመርያ ሳይረዱ ለራሳቸውም ሳያውቁት በከባድ የጭፍን ጥላቻ ውስጥ እራሳቸውን የሚያሰቃዩ እና ቤተክርስቲያኒቱን በሥራ ባሕል አስተምሮ ሊተቹ ሲሞክሩ ያስገርማሉ።

መጀመርያ በቤተክርስቲያኒቱ አጥር ስር ደጋግሞ በማለፍ ወይንም አባቴ ቄስ ነበር ወዘተ በማለት አንድም ቀን ሌላው ቢቀር እንደ "ምሑር" ቤተክርስቲያኒቱን ሳያጠኑ የቡና ላይ ትንታኔያቸው ባዶ ጩኸት ሆኖ እራሳቸውን ያደነቁሩበታል:: ልማት ከማኅበራዊ መስተጋብሩ ጋር ያለው ቁርኝት አይገለጥላቸውም::የቤተክርስቲያን ችግር አስተምሯዊ፣ስርዓታዊ ወይንም የሥራ ባሕል ያልተከለች መሆን ሳይሆን ከግማሽ ክፍለዘመን በላይ በኢትዮጵያ የፖለቲካ መድረክ ላይ የተቀያየሩ መንግስታት የሙስና እና ሃይማኖት የለሽ ወይንም ቀሳጭ እንቅስቃሴ የቤተክርስቲያን አስተዳደር እንዲበላሽ በር መክፈቱ ብቻ እንደሆነ ገና አልበራላቸውም። የአስተዳደር መበላሸት የመሰረተ ዕምነት እና የቤተክርቲያኒቱ ዋና አንኳር መርህ ችግር አይደለም።

የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ዋና የሥራ መርህ እግዚአብሔር ለአዳም ያዘዘው 'ጥረህ ግረህ በወዝህ ብላ' የሚለው ትዕዛዝ ነው።ቤተክርስቲያን መነኮሳቷ ወደገዳም ሲመጡ እንዲያነቡት እና እንደ አንድ ተሞክሮ ተምረውት እንዲገቡት የምታደርጋቸው መጻሕፍት (መጽሓፈ መነኮሳት) ሥራ አምላካዊ ትዕዛዝ ብቻ ሳይሆን ከኃጢአት መራቅያ አንዱ መንገድ መሆኑን አበክሮ ያስተምራል፣ያስጠነቅቃል፣በብዙ የቀደሙ የመነኮሳት ተሞክሮዎች ጭምር ያስተምራል።ቤተክርስቲያኒቱ በሰንበት ዕለታት ህዝቡን ከረፋዱ ሦስት ሰዓት (በአገር ቤት ያለው የቤተክርስቲያን አገልግሎት) ሁሉን አጠናቃ ወደ ቤቱ ታሰናብተዋለች።ቀኑን እንዴት እንደሚውል መወሰን የህዝቡ ፈንታ ነው።

የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን በህዝቡ የሥራ ባሕል ላይ አዎንታዊ አስተምሮ እንዳላት ይህም በጥናት የተረጋገጠ መሆኑን በአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ የሶሾሎጂ ዲፓርትመንት መምሕር እና ተመራማሪ ዶ/ር የራስ ወርቅ የጻፏቸውን ጥናቶች መመልከት፣በዓላት ላይ መምህር ዲ/ን ብርሓኑ አድማሴ የጻፈው ጥናታዊ መጽሓፍ ማንበበ በትንሹ ዓይን ይገልጣል። ከእዚህ ባለፈ ከቡና ላይ ወሬ ይልቅ እንደምሑር ተነስቶ ማጥናት ነው።የልማት ጥናት በድፍን የቡና ላይ ወሬ አያምንም።መሬት ወርዶ ማጥናት ለእዚህም በቂ አቅም መኖር ይጠይቃል። ከጥናታዊ አካሄድ ውጭ በግምት ያውም አንድ መጽሓፏን እንደ ምሑር መባል ሳይመረምሩ በአጥሯ ስር ስላለፉ ወይንም አባቴ እዚህ ቤተክርቲያን አገልጋይ ሆኖ ቤተክርስቲያኒቱን እቤት ውስጥ በሚወራ ወሬ አውቃታለሁ የሚሉ የትንተና መነሻዎች ትዝብት ላይ ይጥላሉ።ላሊበላ በወሬ አልተገነባም፣የኢትዮጵያ በሺህ የሚቆጠሩ የጥልቅ ዕውቀት ምንጭ የሆኑትና አሁን በኢትዮጵያ ገዳማትም፣በውጭ አገር ሙዚየሞችም የሚገኙ የሕግ፣የፍልስፍና፣የስነከዋክብት፣የህክምና እና የሃይማኖት ግዙፍ ጥራዝ መጻሕፍት ቡና በማንቃረር የተጻፉ አይደሉም።የቤተክርስቲያኒቱ  የሥራ ባሕል መሰረት ያደርጉ አባቶች ጊዜያቸውን ሥራ ላይ አውለው የሰሯቸው የሥራ ውጤቶች ናቸው። በማናውቀው፣ባላጠናነው እና በአግባቡ ባልመረመርነው ጉዳይ አውሮፓ እና አሜሪካ ሰርተፍኬት አግኝተን ስለመጣን ወደ ጥልቅ የድንቁርና አዘቅት ውስጥ በግምት መግባት የለብንም። ገባ ብሎ መመርመር፣ማንበብ እና መመልከት ይቅደም።አባቶቻችን ''ከመጠምጠም መማር ይቅደም '' የሚሉት ለእዚህ ነው።

ከእዚህ በታች በአንድ ገዳም ውስጥ ያለውን የሥራ ባሕል የሚያሳይ ልዩ ሪፖርት ይመልከቱ።




 

Saturday, August 13, 2022

በኢትዮጵያ ኦ/ተ/ቤ/ክርስቲያን ሰንበት ትምሕርትቤቶች ማደራጃ መምሪያ ስር የሚገኘው ማኅበረ ቅዱሳን የቤተክርስቲያኒቱንት ዝማሬ ለውጪው ዓለም እንዲደርስ የመጀመርያውን የእንግሊዝኛ መንፈሳዊ መዝሙር አስመርቋል።

Ethiopian Orthodox Tewahido Church Sunday School department releases Spiritual Songs in English
ከመዝሙሮቹ ውስጥ አንዱን እና የምረቃውን ስነሥርዓት ቪድዮዎች ከእዚህ በታች ይመለከቱ።

Proclaim His Name... Testify his works to the world ተናገሩ ድንቅ ስራውን መስክሩ፣ታምሩን ለዓለም ንገሩ


የምረቃ ሥነ ስርዓት ሙሉ ቪድዮ 





Thursday, August 11, 2022

Historical speech - Today, Ethiopia launches Electric power production from the second GERD turbine. Here is the full speech of H.E.Prime Minister Abiy Ahmed on the launching ceremony.

የዓባይ ግድብ ሁለተኛ ተርባይን ስራ ማስጀመርያ የምረቃ ሥነስርዓት ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ያደረጉት ንግግር
ኢቢሲ ቪድዮ


Tuesday, August 2, 2022

ኢዶእ - የትግራይ ሕዝብ በሕወሃት ላይ እንዲነሳ ጥሪ ያደረገ አዲስ ዘፈን የሕወሃትን መንደር አተራምሶታል፣የድምጻዊ ጎይቶም ኃይለማርያም አዲስ ዜማ ምሽቱን ተለቋል። (ቪድዮውን ይመልከቱ)

New music, in Tigrigna, is calling the Tigray people to remove the TPLF regime from its regional power. The music is moving the whole Tigray. The title of the music is EDOI.
ከትግርኛው ስንኞች ውስጥ እንዲህ የሚል ይገኝበታል።

ለሃምሳ ዓመት
እነሱ ባለቤት እኛ ተከራዮች በነሱ ቤት የምትነቃ ንቃ ኣትሞኝ እንዳጠቃ እረፍት የለም እነዚህን (ወያኔን)ሳንሸኝ ወያኔን ሳንሸኝ ጭካኒያቸው በጅምላ የበደሉን በጅምላ የጨረሱን ክምድር ነው ወይስ ከስማይ ስልጣናቸው የወጣቱን ደም ማፍሰሳቸው



ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።