Sunday, May 17, 2015

ደብረ ሊባኖስ እና ትኩረት ያልተሰጠው ግንቦት 13 የሰማዕታት ቀን (የቪድዮ ምስክርነት)

ደብረ ሊባኖስየአቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም በየዓመቱ ግንቦት 12 የፃድቁ የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ፍልሰተ አፅም ዓመታዊ በዓል ይከበርባታል።በማግስቱ ግንቦት 13 ቀንም ብዙ ጊዜ ትኩረት የማይሰጠው ታሪካዊ ቀን ነው።ፋሽሽት ጣልያን ኢትዮጵያን በወረረበት ወቅት ከሶስት መቶ በላይ መነኮሳት በአንድ ቀን የፈጀበት ዕለት።

ከእነኝህ ሰማዕታት ውስጥ እውቁ የቀዶ ጥገና ሐኪም፣የቀዳማዊ አፄ ኃይለ ስላሴ የግል የጤና ዶ/ር  የነበሩት በኃላም የመአሕድ ፕሬዝዳንት ፕሮፌሠር አስራት ወልደየስ አባት ይገኙበታል።ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ አባታቸውን
ጣልያን ደብረ ሊባኖስ ገዳም ውስጥ ሲገድልባቸው የዘጠኝ ዓመት ልጅ ነበሩ።ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ በኢህአዴግ እስር ተፈርዶባቸው በእስር ቤት በህመም ሲሰቃዩ ቆይተው በሕይወታቸው መጨረሻ ላይ ለህክምና ወደ አሜረካ እንዲሄዱ በተደረጉ በቀናት ውስጥ ሕይወታቸው ማለፉ ይታወቃል።

ከእዚህ በታች የምትመለከቱት ፊልም ፋሽሽት ሀገራችንን በወረረ ወቅት በሕይወት የነበሩ አባትን ምስክርነት ያሳያል።
ቪድዮ - ከሰማዕቱ እስጢፋኖስ ገፅ




ጉዳያችን GUDAYACHN BLOG

No comments:

7ኛው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ግንቦት 24፣2018 ዓም በከፍተኛ የሕዝብ ተሳትፎ ተጠናቋል።

ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ በሰባተኛው ብሔራዊ ምርጫ ድምፅ ሲሰጡ። ስለምርጫው ዝርዝር ጉዳይ ምን ያውቃሉ? ✓ ሰባተኛው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ 42 ፓርቲዎች እና 73 የግል ተወዳዳሪዎች ለተለያዩ ምክር ቤቶች ዕጩዎች ...