ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Saturday, May 22, 2021

ከትግራይ፣መተከል፣ሰሜን ሸዋ እና ምዕራብ ወለጋ ለተፈናቀለው ሕዝብ ለመድረስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋኅዶ ቤተክርስቲያን በፍጥነት ልትሰራቸው የምትችላቸው አምስት ስራዎች አሉ

ጉዳያችን/Gudayachn

የትግራይ ሕዝብ ህወሓት ለአርባ ዓመታት ካሰቃየው በኃላም ዛሬም የተረፈው ቡድን እየተሹለከለከ ገበሬውን እየገደለ።ንብረቱን እየቀማው ነው።በመሆኑም ጥቂት ቅምጥሎች በስሙ የኖሩትን ሕይወት እየሰማ ዛሬም መልሶ ችግር ላይ መውደቁ ከተሰማ ሰንብቷል።በእርግጥ ከሕግ ማስከበሩ ሥራ ተከትሎ የፌድራል መንግስት ከ40 ቢልዮን ብር በላይ ወጪ አድርጎ የሰብአዊ ድጋፍ እና መልሶ ለማቆም ጥረት ማድረጉን የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ዛሬ ግንቦት 14/2013 ዓም በቦሌ ክፍለ ከተማ ከሚኖሩ የክልሉ ነዋሪዎች ጋር ባደረገው ውይይት ላይ መገለጡን የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን በዜና ሰዓት ላይ አቅርቧል። ከእዚሁ ባለፈ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ እና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ፣ የክልል አመራሮች፣የአማራ እና የትግራይ ክልል አመራሮች እና ባለሀብቶች  በተገኙበት ሕዝቡን መልሶ ወደ ቀዬው ለመመለስ እና በአማራ እና የትግራይ ክልል መሃል የህዝብ ለሕዝብ ማቀራረብ ስራዎችን የሚሰሩ የሀገር ሽማግሌዎች ያሉበት 14 አባላት ያሉት ሀገር አቀፍ ኮሚቴ ተመስርቷል።

በሌላ በኩል በትግራይ የሲቪሎች መገደል በተመለከተ የአቃቢ ሕግ የራሱን ማጣራት አድርጎ 110 ሲቪሎች መገደላቸውን ማጣራቱን ገልጧል።ግድያው በኤርትራ ወታደሮች መፈፀሙን ይገልጣል።ይህ በእንዲህ እያለ በትግራይ የተፈፀሙት የመደፈር ወንጀሎችም መፈፀማቸውን በሰብዓዊ መብት ድርጅቶችም ሆነ በራሱ በመንግስት ማጣራት ተገልጧል።በእዚህ መሰረት ከኢትዮጵያ ወታደሮች በእዚህ ተግባር ተሰማርተው ነበር የተባሉትን መንግስት አጣርቶ ክስ የመሰረተባቸው እንዳሉ ተገልጧል።

ከመተከል፣ሰሜን ሸዋ እና ከምዕራብ ወለጋ የተፈናቀሉ የአማራ ተወላጆችም ችግር ቀላል የሚባል አይደለም።በቅርቡ የአማራ ክልል እንደገለጠው ከግማሽ ሚልዮን በላይ ሕዝብ መፈናቀሉን ማስታወቁ ይታወቃል።ይህ ሁሉ ሕዝብም በቶሎ ወደ ተፈናቀለበት ቦታ መመለስ አለበት።ምክንያቱም አንገብጋቢው ጉዳይ ህዝቡ ዕለታዊ እርዳታ በቶሎ አግኝቶ ከመጪው ሰኔ አጋማሽ በፊት የእርሻ ስራውን እንዲጀምር የማድረጉ ሥራ ነው።ለእዚህ የተቀደሰ ተግባር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ከሁሉ ቀድማ ልትሰራው የሚገቡ አምስት ተግባራት አሉ። ከሁሉም ቦታ የተፈናቀለው  ሕዝብ ወደ ቀዬው እንዳይመለስ ደባ እየሰሩ ካሉት ውስጥ የህወሓት ደጋፊዎች በዋሻ እና በውጭ ያሉት ሁሉ ናቸው።ምክንያቱም ህዝቡ ከቤቱ ከተበተነ ለነገ ግጭት ሊጠቀሙበት ይፈልጋሉና ነው።

አሁን የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ልትሰራቸው የሚገቡ አምስት ተግባራት አሉ። እነርሱም -

1)  በኢትዮጵያም ሆነ በውጪ ሀገር የሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አጥብያዎች እና ገዳማት በሙሉ በሁለት ሰንበት የሚሰበሰበው ገንዘብ በሙሉ ለተፈናቀሉት ወገኖች እንዲሆን መወሰን እና ወደ ተግባር መግባት፣

2) በሁለት ሰንበታት ከሁሉም አጥብያዎች እና ገዳማት የሚሰበሰብ ቁሳቁስ እና አልባሳት ማሰባሰብ 

3) ይህንን የሚያስተባብሩ ከብክነት የሚጠብቁ እና እርዳታው ወደተፈናቃዮች እስከሚደርስ የሚያስተባብሩ በብሔራዊ ደረጃ መምረጥ እና ማስተዋወቅ፣

4) የእርዳታው አሰባሰብ እና አሰጣጥ ሪፖርት በሚገባ ለሕዝብ ግልጥ ማድረግ እና 

5) በውጭ የሚኖሩ ምእመናኖቿ የሚሳተፉበት በኢትዮጵያ ቴሌቭዥን የሚተላለፍ  የአንድ ምሽት የቀጥታ ጎፈንድሚ እና የገንዘብ ማሰባሰብያ ዝግጅት ማድረግ እና በዝግጅቱ ላይ ሊቃነ ጳጳሳት፣ሰባክያን እና መዘምራን  እንዲሳተፉ በማድረግ ከሚልንየም አዳራሽ ማስተላለፍ የሚሉት ናቸው።

እነኝህን የዕርዳታ ስራዎች ቤተክርስቲያን በቶሎ እንድትሰራቸው ግፊት ማድረግ የቤተክርስቲያን መንፈሳዊ ግዴታ ስለሆነ ብቻ ሳይሆን ከብዙ አቅጣጫ እጅግ መፍጠን አለባት።
 ********************************
ማስታወቂያ /Advertisement 
====================
Click the link below to Top-up your friends or family's mobile air time.
በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ ሂሳብ ሊሞሉ እንደሚችሉ ያውቃሉ? 
አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ - 

No comments: