ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Thursday, January 3, 2013

ፕሮፌሰር መስፍን የዛሬ አራት አመት ቦስተን ላይ ያደረጉት ንግግር ለዛሬዎቹ የ አዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ ተማሪዎችም ሆነ ለ ትውልዱ (ቪድዮ)

 
አዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ዛሬ 40 አመት ያነሳው የነበረው ጥያቄ መላው ኢትዮጵያን ጥያቄ ነበር። ዛሬ ግን ዩንቨርስቲው ኢህአዲግ ፖሊሲ መሰረት ብሔር ድርጅቶች እንዲደራጅ ሆኗል። ማንኛውም ተማሪ ፣የ ወዘተ አባል መሆን እና እነኚህ ብሔር ድርጅቶች ስብሰባ ላይ መገኘት ነገ ተመርቆ ሥራ ለመያዝ ቅድመ ሁኔታ ተደርጎ ተማሪው የቀረበለት የመከፋፈል ድግስ ነው።

ቀድሞው አዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ሲነሳ ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያምን ማንሳት ተገቢ ነው።ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም 1960 ዎቹ ነበረው ለውጥ ትውልድ አካል ነበሩ።በ ኢትዮጵያ ሰብአዊ እና ፖለቲካ መድረክ በተለይ ባለፉት ሃያ አመታት ጉልህ ሚናቸው ታይቷል። ሕንዱ ፑንጃብ ዩንቨርሲቲ እና አሜሪካው ክላርክ ዩንቨርስቲ የተመረቁት ፕሮፌሰር መስፍን አዲስ አበበ ዩንቨርስቲ ጆግራፊ ዲፓርትመንት መሪ፣የ ኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉባኤ መስራች እና ሊቀመንበር ቅንጅት መስራችም ነበሩ። በ 1939 ዓም የድቁና ማዕረግ መቀበላቸውን የሚናገሩም አሉ።

እስኪ አራት አመት በፊት ቦስተን ላይ አድርገውት የነበረው ንግግር ዛሬ ላለነው ትውልድም ጠቃሚ ስለመሰለኝ አቡጊዳ ዩቱብ ላይ ያገኘሁትን ላካፍላችሁ ወደድኩ። ንግግራቸው ያሉብንን ባህል ችግሮች፣እራሳችንን መጠየቅ ያለብንን ጥያቄ፣የ ኢትዮጵያን መሰረታዊ ችግሮች ይዳስሳል እና ጊዜ ወስደው እስከመጨረሻው ያዳምጡት።

 

No comments:

ህወሓት ሰሜን ወሎ ራያን ወርሮ የገጠር ወረዳዎችን እየዘረፈ ነው። ህዝብ ሲዘረፍ እና በአስር ሺዎች ሲፈናቀሉ የመንግስት የፖለቲካም ሆነ የወታደራዊው አመራሮች ዝምታቸው ከተጠያቂነት አያድናቸውም።

በሰሞኑ የህወሓት ወረራ ቆቦ ተፈናቅለው የገቡ የሰሜን ወሎ ተፈናቃዮች  በከፊል ፎቶ፡ ቢቢሲ ሚያዝያ 20፣2024 እኤአ ''ቅጥ አምባሩ የጠፋው'' የፕሪቶርያው ውል   ''ስኩዌር ዋን&#...