Wednesday, December 26, 2012

ዛፍ መሆን ወንበር ከመሆን ይሻለናል።

ከ ፅሁፉ በታች የምታዩት ዛፍ ቀድሞ የነበሩት ጓደኞቹ- (ዛፎች) የት ሄዱ? አልኩ እና ምናልባት ዛፍነታቸውን እረስተው ሌላ መሆን ፈልገው ትተውት ሄደው ይሆን? ብዬ አሰብኩ። እናም ዛፉ ታሪክ እንዲህ መሆን አለበት አልኩኝ። እዚህ በፊት ዛፍ ሆነው መርከብነት፣ለ ታቦትነት ወዘተ ስለተመረጡ ዛፎች ታሪክ አውቅ ነበር።እኔ ግን ዛሬ ታሪኩን መቀየር አማረኝ። ዛፉ ከሚቆረጥ ዛፍ እንደሆነ ቢፀናስ? ብዬ አሰብኩ እና እንዲህ ጫጫርኩት።
 ይህ ዛፍ ድሮ ብዙ ዛፎች አብረውት ነበሩ። ሌሎቹ ዛፎች ዛፍ መሆናቸውን ትተው ወንበር፣በር፣ወዘተ መሆን አማራቸው።እናም ዛፍ የመሆን ክብራቸውን ለወጡት።

''ዛፍ ሆነን ከሜዳ ላይ ከሚበርደን ቤት ገብተን ወንበር ሆነን ሰዎች ክብር አዋርደው ቢቀመጡብን፣በር ሆነን እንደፈለጉ ቢወዘውዙን ይሻላል'' ብለው አምላክ የሰጣቸውን ዛፍነት ክብር ተዉት።

ይህ ዛፍ ግን ብቻውን ቆሞ ሁሉም ሲሄዱ ታዘባቸው።

በመጨረሻ እንዲህ ሆነ

በመጨረሻ ግን ሃገሩ የተገኘ ብቸኛ ዛፍ ነው እና የሃገሩ ሰዎች ተሰብስበው ቤተክርስቲያን ሊሰሩ ሲያስቡ እስከመጨረሻ ወደ ጸናው ዛፍ መጡ። አከበሩትም ቤተክርስቲያን ጎኑ ሰሩ።ዛፉም ቤተክርስቲያኑ ቅፅር ግቢ ውስጥ ተከለለ። ቀጥሎም አንድ ቀን የኔታ ወደ ዛፉ መጡ። ብቻውን የቆመባቸውን እነኛን ክፉ ዘመናት አስበው ተከዙ። ተክዘውም አልቀሩም።የሚያስተርምሯቸውን ተማሪዎች ዛፉ ስር ለማድረግ ወሰኑ። ከዛፉ የተሻለ ስለ ፅናት የሚያስተምር ምሳሌ እንደማይገኝ አውቁ። አስበውም አልቀሩ የኔታ ወንበራቸውን ዛፉ ስር ዘረጉ። እነሆ ዛፉ በእራሱ አርጅቶ ካልወደቀ በቀር እንደማይቆረጥ ቁርጥ ሆነ። ሌሊት ማህሌት፣ ማለዳ ቅዳሴ፣ የቀን ቅፀላ ምግቡ ሆነ። ''እስከመጨረሻ የሚፀና እርሱ ይድናል'' የሚለውን ቃል አሰበ። ቀድሞ ወንበር እና በር ለመሆን ዛፍነታቸውን የከዱ የድሮ ጓደኞቹ ቀኑበት። አሁን እነርሱ ወንበርነታቸው አብቅቶ ከደጅ ተጥለው ማገዶነት የሚመጣውን አመት በዓል ይጠባበቃሉ። እስከመጨረሻ የፀናውን ዛፍ ያድርገን።ዛፍ መሆን ወንበር ከመሆን ይሻለናል።

እነሆ ዛፉ ታሪክ ተፈፀመ።

ጌታቸው

ኦስሎ

 

2 comments:

Teklu said...

This is superb. I prefer to be the tree, hence my name_ Teklu.

Teklu said...

This is superb. I prefer to be the tree, hence my name_ Teklu.

የክፍለዘመናችን የኢትዮጵያ የስልጣኔ ማማ መለኪያ የሆነው ታላቁ የኢትዮጵያ ጉባዔ ነገ በአዲስ አበባ ይከፈታል። ህልውናችን፣መጪው ስልጣኔያችን፣ሰላማችን እና ዕድገታችን በእዚህ ጉባዔ ውጤትና ሒደት ይወሰናል።

Foto : Fana digital  የቻልን በሀሳብ እና በጸሎት፣ ያልገባን እና የተምታታብን ደግሞ እኪገባን በዝምታ በመቆየት ኢትዮጵያን እናግዛት። ========= ጉዳያችን ልዩ ========= ኢትዮጵያ ሐምሌ 8፣2018 ዓም...