Sunday, September 11, 2016

´የጥፋት ዘመን´ የተሰኘ በጋዜጠኛና ደራሲ ሙሉቀን ተስፋው በዐማራ ሕዝብ ላይ የተፈፀመ የዘር ማፅዳት የሚያጋልጥ ጥናታዊ መፅሐፍ ገበያ ላይ ነው

የመጽሐፉ የፊት ሽፋን  
´´ወጣቱ ጋዜጠኛና ደራሲ ያቀረበልን በማያሻማ መረጃ የተደገፈ መጽሐፍ ታሪካዊና ወቅታዊ ነው´´  ዶ/ር አክሎግ ቢራራ 
´´ይህ መጽሐፍ ማንኛውም የኢትዮጵያ ህልውና የሚያሳስበው ሰብዓዊ ፍጡር ሊያነበው የሚገባ ነው።´´ዶ/ር አሰፋ ነጋሽ 
291 ገፆችን የያዘው ይህ መጽሐፍ በዐማራ ሕዝብ ላይ ከ1983 እስከ 2007 ዓም ድረስ የተፈፀሙትን ግድያዎች እና እንግልቶች በማስረጃ አስደግፎ ያሳያል።
በ1967 ዓም በማነፌስቶው ላይ የዐማራ ሕዝብን በጠላትነት መፈረጁን በግልፅ ያሳወቀው ሕወሓት ላለፉት 25 ዓመታት የፌድራል ሕጉ እንዲኮላሽ ከማድረግ ጀምሮ ምን ሲያደርግ እንደነበር በግልፅ እና በዝርዝር ያስረዳል።
ለወደፊቷ ኢትዮጵያ ይህ ክፉ ተግባር እንዳይደገም ሁሉም ዜጋ ቢያነበው ኃላፊነት እንዲሰማው ያግዛል።
መጽሐፉ  በአውሮፓ እና አሜሪካ በከፍተኛ ደረጃ ተነባቢነት እያገኘ ነው። የመፅሐፉ አዘጋጅ እና ፀሐፊ ጋዜጠኛ እና ደራሲ ሙሉቀን ተስፋው ለኢሳት የሰጠው ቃለ መጠይቅ ከእዚህ በታች ባለው ቪድዮ ይመልከቱ።


ጉዳያችን GUDAYACHN www.gudayachn.com

No comments:

በአቴንስ፣ግሪክ የምትገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን ላለፉት 40 ዓመታት በላይ ስትጠቀምበት የነበረውን ፖሊጎኖ የሚገኘው ቤተክርስቲያን በፖሊስ ታሸገ።የቅዱስ ሲኖዶስ አፋጣኝ ምላሽ እየተጠበቀ ነው።

የአቴንስ ኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን የታሸገችበት የጉግል የእንግሊዝኛ ትርጉም እና የግሪክኛ ዋናው ኮፒ። በግሪክ አቴንስ የምትገኘው እና ወደ ግማሽ ክ/ዘመን አገልግሎት ስትሰጥ የነበረችው እና በአቴንስ ፖሊጎኖ የምትገኘው የ...