ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Sunday, September 22, 2019

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንና በምዕመኖቿ ላይ የሚፈጸመው ግፍና መከራ እንዲቆም፣ ዛሬ ዕሁድ ብቻ ከሰላሳ በላይ በሚሆኑ የኢትዮጵያ ከተሞች ሰልፍ ተደረገ።የሙስሊሙ ማኅበረሰብ ሰልፎቹን ተቀላቅሏል።ለንደንም ሰልፍ ነበር።(ከሃያ በላይ ፎቶዎች ይመልከቱ)

Breaking news ethiopia ሰበር ዜና ኢትዮጵያ 

in over thirty cities in ethiopia, Hundred Thousands TAKE TO STREETS TO PROTEST REPEATED ATTACKS AGAINST Ethiopian orthodox tewahido church (see over 20 pictures)

Today Ethiopian Orthodox Tewahido church followers and religious leaders have another round huge demonstration, protesting burning of the churches and repeated attacks on its followers, was held in over thirty cities in Ethiopia and in London. Last thursday,there was similar demonstration in Washington DC in front of Ethiopian Embassy. Muslim Ethiopians have also joined in all demonstrations showing their solidarity with Ethiopian christians.(see photos below Amharic version)
ጉዳያችን ዜና / Gudayachn News
 መስከረም 11/2011 ዓም (ሴፕቴምበር 22/2019 ዓም)
=================
 የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ምእመናን እና አባቶች በቤተ ክርስቲያንና ምዕመኖቿ ላይ ግፍ የፈጸሙት አካላት በሕግ እንዲጠየቁ፣በቤተ ክርስቲያን ላይ የሚደረጉ ጥቃቶች እንዲቆሙ እና መንግስት ለችግሩ ትኩረት እንዲሰጥ በመጠየቅ  ከሰላሳ በላይ በሚሆኑ የኢትዮጵያ  ከተሞች ዛሬ  ሰልፎች ተካሂደዋል።
በያዝነው ሳምንት አጋማሽ ላይ በዋሽንግተን የሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን እና አባቶች በኢትዮጵያ ኤምባሲ ፊት ለፊት ሰልፍ ያደርጉ ሲሆን ዛሬ በለንደን ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሕዝብ በተገኘበት ሰልፍ መደረጉን ለማወቅ ተችሏል።በሀገር ቤት የተደረገው ሰልፍ ከሰላሳ በላይ በሚሆኑ ከተሞች የተደረገ ሲሆን ከእነኝህ ውስጥ  በባሕር ዳር፣ በደብረ ማርቆስ፣ በብቸና፣ በደጀን፣ በሞጣ፣ በደብረ ብርሃን፣ በማጀቴ፣ በጫጫ፣ በአረርቲ፣ በመሐል ሜዳ፣ በፍኖተ ሠላም፣ በቡሬ፣ በመርዓዊ፣ በእንጅባራ፣ በደባርቅ፣ በዳባት፣ በአዲ አርቃይ፣ በጯሂት፣ በወልድያ፣ በቆቦ፣ ሮቢት፣ በላልይበላ፣ በውጫሌ፣ በወረኢሉ፣ በደላንታ፣ በኮን፣ በዳንግላ፣ በዱር ቤቴ፣ በአዲስ ዘመን እና በሌሎችም ከተሞች ተካሂደዋል፡፡
በልዩ ልዩ ከተሞች የተደረጉ ሰልፎች ፎቶዎች ከእዚህ በታች ይመልከቱ።
Ethiopia
Ethiopia
Ethiopia
Ethiopia

Ethiopia
Ethiopia

Ethiopia

Ethiopia
Ethiopia
Ethiopia
Ethiopia
Ethiopia
Ethiopia
Ethiopia
Ethiopia
Ethiopia
Ethiopia
Ethiopia
Washington DC


London
ለንደን /London

ለንደን /London


ጉዳያችን GUDAYACHN 
 www.gudayachn.com

No comments:

ህወሓት ሰሜን ወሎ ራያን ወርሮ የገጠር ወረዳዎችን እየዘረፈ ነው። ህዝብ ሲዘረፍ እና በአስር ሺዎች ሲፈናቀሉ የመንግስት የፖለቲካም ሆነ የወታደራዊው አመራሮች ዝምታቸው ከተጠያቂነት አያድናቸውም።

በሰሞኑ የህወሓት ወረራ ቆቦ ተፈናቅለው የገቡ የሰሜን ወሎ ተፈናቃዮች  በከፊል ፎቶ፡ ቢቢሲ ሚያዝያ 20፣2024 እኤአ ''ቅጥ አምባሩ የጠፋው'' የፕሪቶርያው ውል   ''ስኩዌር ዋን&#...