Pages

Pages

Saturday, November 30, 2013

በእዚህ ዘመን ካሉት ከአዋቂዎቹ ይልቅታዳጊ ህፃናቱ የኪነጥበብ ባለሙያዎች የተሻለ የሀገር ፍቅር ያንፀባርቃሉ(ቪድዮ)

በእዚህ ዘመን አርቲስቶቻችን በእራሳቸው ምህዋር ውስጥ እየዞሩ ሀገራቸውን ባብዛኛው የዘነጉበት፣ለሙያ፣ለእውነት እና ለሕዝብ ፍቅር ከሚሰሩ ስራዎች ይልቅ ብዙ ብር የሚያስገኙ ስራዎች የተወደዱበት እና በሕዝብ ከመወደድ ይልቅ ከሚሊንየሮች ጋር ሸራተን መታየት የበለጠባቸው ዘመን እየሆነ ነው።እርግጥ ነው እንደ እነ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) አይነቶች በባትሪ ተፈልገው የተገኙ አልጠፉም።ኢትዮጵያ ግን የጥበብ ስራዋ በእዚህ አይነት ደረጃ ህዝብን እና ብሔራዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ስራዎች የወደቁበት ወቅት አሁን ነው።

እዚህ ላይ የኢትዮጵያ የኪ-ነጥበብ   እድገት እና ውድቀት ትንተና ላይ አይደለሁም።ሕዝብን፣ሃገርን የተመለከቱ ያለፈውን እና መጪውን የሚያማትሩ ስራዎች ግን በፈጣን ገንዘብ አስገኚ ስራዎች ተተክተዋል።ፊልሞች ወጣቶችን በፍቅር ታሪክ በማማለል ተሳክቶላቸው ይሆናል።ወጣቶቹ ወዴት እንደሚሄዱ፣ከየት እንደመጡ፣የጋራ ሃገራዊ እሴታቸው ምን እንደሆነ ግን አይነግሩም።ይህ በጣም ጥቅል እና በወፍ በረር የታየ ሃሳብ ይሆናል።በእዚህ ዘመን ካሉት አዋቂዎቹ ታዳጊ ህፃናቱ የኪነጥበብ ባለሙያዎች የተሻለ የሀገር ፍቅር ያንፀባርቃሉ።

ለናሙን ከእዚህ በታች ያሉትን የሸገር ራድዮ ለወጣት ሴቶች በራስ መተማመን ዙርያ የሚያስተምርበት ''የኛ'' የተሰኘ ተከታታይ ተውኔት ላይ የሚሰሙ ዜማዎች ናቸው። ቀደም ብሎ የወጣው ''አቤት'' የተሰኘው ዜማ የ2005 ዓም የዓመቱ ምርጥ ዜማ ተብሎ በሕዝብ ተመርጧል።በቅርቡ በተቀረፀው ''እቴጌ'' በተሰኘው ዜማ  ላይ ደግሞ ታዳጊ ህፃናቱ አስቴር አወቀ እንድትሳተፍበት አድርገዋል።ይመልከቷቸው።





No comments:

Post a Comment

አስተያየትዎን እዚህ ላይ ይስጡ