Sunday, November 17, 2013

በዛሬውም ሆነ በመጪው ትውልድ የሚጠየቁ ሁለት ''ለምኖች''



1/ ለምን አንድ 


ኢትዮጵያውያን  በሳውዲ ባሉ ወገኖቻችን ችግር  ላይ ከዋሽግተን እስከ አውስትራሊያ ሰልፍ ሲሰለፉ ለምንድነው በየሀገሩ ያሉ  የኢትዮጵያ ኢምባሲዎች በሰልፉ ላይ ያልተገኙት? ወይንም  ለምሳሌ የዛሬውን የዋሽግተን ሰልፍ አስመልክቶ  ቪኦኤ  ለዋሽግተን ኢትዮጵያ ኢምባሲ ቢደውልም ምላሽ አላገኘሁም ብሏል። ይህ የሀገራችን ጉዳይ አይደለም እንዴ? ሰልፉ የሳውዲ ኤምባሲን  ያስከፋው እንጂ የኢትዮጵያን ኢምባሲ ከሰልፉ ጋር እንዳይተባበር የሚያደርገው ምን አይነት ሐረካት ነው?

2/ ለምን ሁለት 


አሁንም በሺህ የሚቆጠር ኢትዮጵያዊ ሲሰለፍ ሳውዲ አረብያን ሲቃወም የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን እና ራድዮ አንዲት እንዳይተነፍስ ያስገደደው ጉዳይ ምንድነው? ለቅሶው ለወገን፣እንባ መራጨቱ ለወገን፣ኢትዮጵይ ቴሌቭዥን ይህንን እነ ቢቢሲ፣ሲ ኤን ኤን፣ዋሽግተን ፖስት  የዘገቡትን የኢትዮጵያውያን የሳውዲ መንግስትን ተቃውሞ ለምን አላሳየም? ለምን? አዲስ አበባ ያለው የሳውዲ ኤምባሲ ሰራተኞች የአረብ ሻሂ ፉት እያሉ ስሙን የሳውዲ ቲቪ መባል እሩብ ጉዳይ የቀረውን ኢቲቪ ሲያደንቁት አይታያችሁም? ግን ለምን? ሼም  ኦን ኢቲቪ! ካለ ምንም ማጋነን ኢቲቪ ወቅታዊ አብሽቅ ነው።

እስኪ ደግሞ መጪውን ትውልድ እናስብ የዛሬ 30 ዓመት አንድ ኢትዮጵያዊ እንበል የዩንቨርስቲ ተመራቂ የመመረቅያ ፅሁፉን ''በኢትዮጵያ እና ሳውዳረብያ ግንኙነት ላይ''ሊሰራ ቢያስብ እና የሰሞኑን ሰልፎች ከቢቢሲ እና ሲ ኤን ኤን ላይ ወስዶ ከጠቀሰ በኃላ ኢቲቪ ስለሰልፎቹ  ምንም አለማለቱን ሲመለከት መደምደምያው ላይ ምን ብሎ ይፅፋል? ''ኢቲቪን የሳውዲ ገንዘብ ተቆጣጥሮት ነበር'' ብሎ? እስኪ አስቡት የት ነን? ማነው የሚገዛን? ያለቀስኩት- ከባዕድ ቆንስላ ፊት። የወቀስኩት- የውጭ መንግስትን። ኢቲቪ ምን ቤት ነው ድምፄን የሚያፍነው? ሳስበው ሳስበው ውስጤን እሬት እሬት አለኝ።

ጉዳያችን
ህዳር 9/2006 ዓም

No comments:

በአቴንስ፣ግሪክ የምትገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን ላለፉት 40 ዓመታት በላይ ስትጠቀምበት የነበረውን ፖሊጎኖ የሚገኘው ቤተክርስቲያን በፖሊስ ታሸገ።የቅዱስ ሲኖዶስ አፋጣኝ ምላሽ እየተጠበቀ ነው።

የአቴንስ ኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን የታሸገችበት የጉግል የእንግሊዝኛ ትርጉም እና የግሪክኛ ዋናው ኮፒ። በግሪክ አቴንስ የምትገኘው እና ወደ ግማሽ ክ/ዘመን አገልግሎት ስትሰጥ የነበረችው እና በአቴንስ ፖሊጎኖ የምትገኘው የ...