ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Friday, November 22, 2013

አስር ጊዜ ከንፈር ከመምጠጥ ኢሳትን መርዳት!


የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቭዥን -ኢሳት ከተመሰረተ ገና ሶስት አመታትን ቢያስቆጥርም በኢትዮጵያ ፖለቲካዊ፣ማህበራዊ እና ምጣኔ ሃብታዊ ጉዳይ ላይ ቁጥር አንድ ተፅኖ ፈጣሪ ሆኖ ወጥቷል።ዛሬ ዛሬ ኢሳት ባይኖር ኖሮ ስንት ሕዝብ ሊሰማቸው የሚገቡ ጉዳዮች ሳይሰሙ ሊቀሩ የመቻላቸውን ሁኔታ ስንመለክት ኢሳት ወሳኝ መሆኑን እንረዳለን።

በቅርቡ ከተከሰቱት የሙስሊሞች ጥያቄ፣በቤንሻጉል የጉርዳፈርዳ ነዋሪዎች መፈናቀል፣ሰሞኑን በሳውዲ አረብያ በወገኖቻችን ላይ የተፈፀመውን ግፍ ለሕዝብ በማድረስ በኩል ሁሉ የኢሳትን ታላቅ የስራ ክንውኖች የሚገልፁ ናቸው።ኢሳትን  ኢትዮጵያን የሚወድ ሁሉ ሊደግፈው የሚገባ ነው።የመረጃ  መታፈን ቁጥር አንድ ሉዓላዊነታችንን የሚያሳጣን መሆኑን የተገነዘበው ስንት ሰው እንደሆነ አላውቅም።ይህንን ስንረዳ የመገናኛ ብዙሃንን አስፈላጊነት እንረዳዋለን።ይህንን በደንብ የተረዳ የስርዓቱ ደጋፊ ቢሆንም ኢሳትን ለመርዳት ግዴታው ነው ብዬ አስባለሁ።ዛሬ ኢሳት እና ኢቲቪ ለሕዝብ በሚያቀርቡት ይዘት ተለያዩ እንጂ ሁለቱም የህዝብ ንብረት ናቸው።

ነገን አማትረን ስናይ ግን ኢትዮጵያ መንገዷ ሲሰምርላት ትልቅ አለማቀፍ የዜና አውታር እንደሚሆኑ አንጠራጠርም።ለእዚህ ሁሉ ግን ዛሬ ላይ ሆኖ ኢሳትን ማገዝ ከኢትዮጵያውያን የሚጠበቅ ትልቅ ቁምነገር ነው።ኢሳት በውጭ ከሚኖረው ሕብረተሰብ ማግኘት የሚገባውን ያህል እያገኘ አለመሆኑ በተደጋጋሚ የተገለፀ ጉዳይ ነው።አሁንም ጥያቄው ስንቶች በወር ሻይ ሲጠጡ ጉርሻ የሚሰጡትን ሃያ ዶላር በአግባቡ ይሰጣሉ? ነው።በቀን 2 ዶላር ብንሰጥ በወር 60 ዶላር መሆኑን ሳንረሳ ማለት ነው።አሁን የተጠየቀው በትንሹ 20 ዶላር ነው።ኢሳት በመጪው እሁድ ህዳር 15/2006 ዓም (ኖቬምበር 24/2013) ''እሳት የእኔ ነው'' የተሰኘ በቀጥታ ስርጭት ልዩ መርሃግብር አዘጋጅቷል።በዝግጅቱ ላይ በቀጣይነት የሚከፍሉ አባላትን ለማፍራት አስቧል።ቢያንስ ከቤት ሆኖ ይህንን መርሃግብር መሳተፍ ትንሿ ማንም ሰው ሊያደርገው የሚችለው ሥራ ነው።አስር ጊዜ ከንፈር ከመምጠጥ ኢሳትን መርዳት።ደግሞ መርዳት አይደለም ግዴታን መወጣት ነው።

ጉዳያችን
ሕዳር/2006 ዓም







No comments:

ህወሓት ሰሜን ወሎ ራያን ወርሮ የገጠር ወረዳዎችን እየዘረፈ ነው። ህዝብ ሲዘረፍ እና በአስር ሺዎች ሲፈናቀሉ የመንግስት የፖለቲካም ሆነ የወታደራዊው አመራሮች ዝምታቸው ከተጠያቂነት አያድናቸውም።

በሰሞኑ የህወሓት ወረራ ቆቦ ተፈናቅለው የገቡ የሰሜን ወሎ ተፈናቃዮች  በከፊል ፎቶ፡ ቢቢሲ ሚያዝያ 20፣2024 እኤአ ''ቅጥ አምባሩ የጠፋው'' የፕሪቶርያው ውል   ''ስኩዌር ዋን&#...