Saturday, November 23, 2013

በዓለም ላይ በሳውዳረብያ በወገኖቻችን ላይ የደረሰውን ሰቆቃ ለመቃወም ሰልፍ የከለከለች ብቸኛ ሀገር-ኢትዮጵያ ነች። ይህ እንቅልፍ ያስወስዳል?

አዲስ አበባ ፌድራል ፖሊስ የሳውዲን መንግስት ለመቃወም ሰልፍ የወጡትን ሲደበድብ 

በዓለም ላይ በሳውዳረብያ በወገኖቻችን ላይ የደረሰውን ሰቆቃ ለመቃወም ሰልፍ የከለከለች ብቸኛ ሀገር-ኢትዮጵያ ነች።
ኢትዮጵያውያን በሳውዲ አረብያ በወገኖቻችን ላይ የደረሰውን ሰቆቃ አስመልክተው

ሰሜን አሜሪካ 

 - የተለያዩ ግዛቶች

 በአውሮፓ-

በጀርመን፣

እንግሊዝ፣

ጣልያን፣

ስዊድን፣

ኖርዌይ፣

 ካናዳ-

የተለያዩ ግዛቶች 

 አውስትራሊያ


መካከለኛው ምስራቅ 

- እስራኤል፣
- ቤሩት 

አፍሪካ 

 ደቡብ አፍሪካ፣

 ዑጋንዳ ፣

እስያ 

 ደቡብ ኮርያ፣

 በሚገኙ የሳውዳረብያ ኤምባሲ ፊት ለፊት ሰልፍ አድርገዋል።በለቅሶ በቁጭት እንባ ተራጭተዋል።ኤርትራውያን ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን አብረው ተሰልፈው ተላቅሰዋል ቁጣቸውን ገልፀዋል።

ቀሪ ሰልፎች ለምሳሌ በቤልጅየም ብራስልስ እና ሌሎችም ሀገሮች ይቀጥላሉ።
በዓለም ላይ የሳውዲን መንግስት ተቃውመው ዜጎች ሰልፍ እንዳይወጡ የከለከለች ብቸኛ ሀገር የጉዳዩ ባለቤት ኢትዮጵያ ብቻ ነች።ሌላ ማንም ሀገር አልከለከለም።

ኢትዮጵያ የሳውዲን ኢ-ሰብአዊ ድርጊት ተቃውመው ሰልፍ የወጡ እንቡጥ እና ለጋ ወጣቶችን፣አረጋውያንን፣አዛውንቶችን በፖሊስ እየደበደበች ብዙዎችን አካለ ስንኩል አደረገች።የቀሩትን  ሰልፉ የተደረገበት ቀን ሳትውል ሳታድር ወደ እስር ቤት ወረወረች።ይህንን የሚቀበል እንዴት አይነት ህሊና ነው?
ኢህአዲግ-ወያኔዎች ሆይ! ይህ ጠረንጴዛችሁ ላይ ያለ ያልተመለሰ ምን ጊዜም ልንረሳው የማንችለው ግን መልስ የሚሻ አጀንዳ ነው።

ጉዳያችን 

ህዳር/ 2006 ዓም 

No comments:

በአቴንስ፣ግሪክ የምትገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን ላለፉት 40 ዓመታት በላይ ስትጠቀምበት የነበረውን ፖሊጎኖ የሚገኘው ቤተክርስቲያን በፖሊስ ታሸገ።የቅዱስ ሲኖዶስ አፋጣኝ ምላሽ እየተጠበቀ ነው።

የአቴንስ ኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን የታሸገችበት የጉግል የእንግሊዝኛ ትርጉም እና የግሪክኛ ዋናው ኮፒ። በግሪክ አቴንስ የምትገኘው እና ወደ ግማሽ ክ/ዘመን አገልግሎት ስትሰጥ የነበረችው እና በአቴንስ ፖሊጎኖ የምትገኘው የ...