ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Thursday, November 21, 2013

በሳውዲ አረብያ ያሉ ወገኖቻችን ጉዳይ ብዙ እርቀት መሄድ ይፈልጋል። ገጠራማው የሳውዳረብያ ግዛት የኢትዮጵያውያንን ሰቆቃ እያስተናገደ ነው።



ሳውዲ አረብያ ያሉ ወገኖቻችን ችግር ገና አልተቀረፈም።እስካሁን ባብዛኛው የታየው በከተሞች አካባቢ ያሉት ነው።ቢጮሁ የማይሰማበት ማንም የማይሰማቸው በገጠራማ የሳውዲ ግዛቶች ያሉ ብዙ ሺህ ወገኖቻችን ድረሱልን እያሉ ነው።ከከተማ እየጠለፉ የሚወስዷቸውን እህቶቻችንን የሚደብቁባቸው ቦታዎች እነኚሁ ከከተማ ራቅ ያሉ ቦታዎች ናቸው።

በኢሳት አስተባባሪነት የተመሰረተው ዓለም አቀፍ ግብረሃይል ለሳውዲ ንጉስ፣የደህንነት እና የፖሊስ መስርያቤት ግልፅ ደብዳቤ ፅፏል።ይህ የስራው መጀመርያ ነው።ግብረ ኃይሉ ከዲፕሎማሲ ሙያ ጀምሮ የተለያየ ሙያ ያላቸው ኢትዮጵያውያንን የያዘ ለእራሳችን ችግር መፍትሄዎቹ እኛው ነን የሚለውን ብሂል በተግባር ያመላከተ ድንቅ ጅምር ነው።በቀጣይ ጊዜ ለሚኖሩ የስራ ዝርዝሮች እንደሚኖሩት ይጠበቃል። የእዚህ አይነቱ ግብረ ኃይል በተጠናከረ መልክ በቀጣይነት ሊኖር የሚገባው እና ለሌሎች ኢትዮጵያን እና ኢትዮጵያዊነትን ለሚገዳደሩ ተግዳሮቶች ሁሉ ምላሽ የሚሰጥ እና አቅም የሚያጎለብት እንዲሆን የሁሉም ኢትዮጵያዊ ኃላፊነት ነው።

በሌላ በኩል ወደሀገር ቤት በመንግስት እየተመለሱ መሆናቸውን ኢቲቪ እያሳየ ነው።ስደተኞቹ በሲቪል ሰርቪስ ግቢ በግዝያዊነት ያረፉ እንዳሉ ተነግሯል። ሆኖም ግን በሺህ የሚቆጠር ኢትዮጵያዊ  ስደተኛ ሃሳሩን ከሚያይባት ሳውዲ አረቢያ መንግስት እስካሁን ሀገርቤት አድርሻለሁ ያለው ቁጥር ግራ እያጋባ ነው።ለምሳሌ  የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ፣የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ትዊተር ገፅ እና ኢቲቪ የተናገሩት የተምታታ ቁጥር ነው።ለምሳሌ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አቶ ዲና  4,961 ወደ ሀገርቤት አስገብተናል ሲሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዶ/ር ቴዎድሮስ በትዊተር ገፃቸው ላይ የተመለሱትን ቁጥር 10,707 ናቸው ብለዋል።ዛሬ ኢቲቪ ደግሞ 13,000 ሰው ተመልሷል ብሏል።በዚህን ያህል ቁጥር የአንድ መንግስት ድርጅቶች እንዴት ይለያያሉ? በቁጥር ነገር መቸም መንግስትን ማመን እንደማይቻል ብዙ ምሳሌዎችን መጥቀስ ይቻላል።

የችግሩ ግዝፈት ግን ወደ ሀገር የማስገባት ሥራ ብቻ አይደለም። በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን በገጠራማ የሳውዲ ግዛቶች ውስጥ ይኖራሉ።በአንድ የዓለም ባንክ በአለማችን ላይ በገጠራማ ቦታዎች የሚኖሩ ህዝቦች ቁጥር በሚያሳይ ዘገባው ላይ ሳውዳረብያ በ 2012 ዓም እ ኤ አ ወደ 5ሚልዮን የሚጠጋ ህዝቧ ከከተማ እርቆ ነው የሚኖረው።(http://data.worldbank.org/indicator/SP.RUR.TOTL) እንግዲህ ስንት እህቶቻችን እና ወንድሞቻችን የሚሰማቸው አጥተው በየገጠሩ ሃሳራቸውን እያዩ ነው? ምን ያህል ኢትዮጵያውያን በሳውዳረብያ እንደሚኖሩ የኢትዮጵያ ኢምባሲ የጠራ መረጃ የለውም። አሁን ብዙዎቻችን ትኩረት የሰጠነው እና ስለችግሩ እየሰማን ያለነው በሪያድ እና ጅዳ አካባቢ ነው።በሌሎቹ አካባቢ ያሉት ወገኖች ጋር ለመድረስ ግን ምናልባት ጥቂት ሳምንታት ብሎም ወራት ልፈልግ ይቻላል።

 በሳውዲ መንግስት ላይ አስፈላጊው ዓለም አቀፍ ተፅኖ ለማድረግ ከተቻለ እና ተከታታይ እረፍት የለሽ ወቀሳዎች ከተሰነዘሩ ሳውዳረብያ ወደመሰላቸቱ ብቻ ሳይሆን በሃገሯ ካለባት ውስጣዊ ችግሮች አንፃር ለችግሩ መፍትሄ የማትሰጥበት ምክንያት የለም።ዓለም አቀፉ የኢትዮጵያውያን ግብረ ኃይል ግን ተከታታይ የስራ ሪፖርቶቹን ለሕዝብ እየገለፀ የራሱ የሆነ በጎ ተፅኖ መፍጠሩ አይቀርም። ከእዚህ በዘለለ በሌሎች የአረብ ሃገራት ላሉት ወገኖችም አንድ አይነት ማዕከልን የጠበቀ እርዳታ ለማድረግም ሆነ መብታቸውን እዲያስከብሩ ገንቢ ሃሳቦችን የማቅረብ ብሎም በየሀገራቱ የሚከራከርላቸው አካል ለመመስረት ይችላል።

ከእዚህ በታች የተለጠፈው የሩስያ ቲቪ (RT) ሳውዲን የተመለከተ ልዩ ዘገባ ሀገሪቱ ያለባትን የውስጥ ችግር ያመላክታል።የሀገሪቱን ኢ-ሰብአዊ አያያዝ ብቻ ሳይሆን የመንግስት መዋቅር ጭምር  ወጣቱ ንጉሳዊው ቤተሰብ የነቀፉበት አግባብን ዘገባው ይጠቁማል።



ጉዳያችን GUDAYACHNgetachewb221@gmail.com

No comments:

ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።