Thursday, October 3, 2013

ሸገሮች መልካም ልደት! ሊባሉ ይገባል



ሸገር ራድዮ ስርጭት የጀመረበት ስድስተኛ አመቱን እያከበረ ነው።የሸገር የመጀመርያ ስርጭት የተጀመረው መስከረም 23/2000 ዓም ነው።
ሸገር -
- ማኅበራዊ ችግሮች የሚቀረፉበትን መንገድ በማመላከት፣
- ወቅታዊ መረጃዎችን በመስጠት እና
- የተዋጣለት ሀገርኛ ዘይቤ የተላበሱ መዝናኛ ፕሮግራሞቹን ለሕዝብ በማድረስ የቀዳሚነቱን ስፍራ እንደያዘ ብዙዎች የሚያወሱለት ነው።
ሸገር -
 - ለአዲሱ ትውልድ ጠንክሮ የመስራት ውጤትን አበክሮ በመንገር፣
 - ኢንዱስትሪያዊ ሰላም እንዲሰፍን ቀድሞ መረጃዎችን ለሚመለከታቸው ሁሉ በመስጠት፣
 - ያለፈውን በእርጋታ የመመልከት እና መጪውን ተስፋ በማመላከት በኩል ሸገር የተዋጣለት ነው።

ይህ ብቻ አይደለም ሸገር ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር! ብሎ መርሃግብሩን የሚጀምር እና የሚጨርስ ብቸኛ ሀገርቤትኛ የመገናኛ ብዙሃንም ነው።

ድምፀ መረዋዋ መዓዛ ብሩ የተዋጣለት የጋዜጠኝነትን ሙያ፣ስነ-ምግባር እና ኃላፊነት ያሳየች የሸገር 102.1 ራድዮ መስራች ነች።

ሸገሮች መልካም ልደት ሊባሉ ይገባል።
የሸገር ድህረ-ገፅ የፊት ገፅ ለመክፈት ይህንን ይጫኑ  - http://www.shegerfm.com

1 comment:

Anonymous said...

sew yehonech sew!!!!!

በጠ/ሚ/ዐቢይና ሙ/ጥ/ዲ/ዳንኤል ላይ በውሸት ወሬ የዘመቱት ''አፈ-ጊንጦች'' በቴዲ አፍሮ ዘፈን ሊሸሸጉ ሲሞክሩ የኢትዮጵያ ሕዝብ እየሳቀባቸው ነው።

ጠ/ሚ/ዐቢይ አሕመድ እና ሙ/ጥ/ዲ/ዳንኤል ክብረት በታላቁ የዓባይ ግድብ ምርቃት ቀን። ======== ጉዳያችን ምጥን ======== አፈ ጊንጥነቱ እና የውርደት ካባው ''አፈ ጊንጥነት'' የሚለውን ...