Thursday, October 3, 2013

ሸገሮች መልካም ልደት! ሊባሉ ይገባል



ሸገር ራድዮ ስርጭት የጀመረበት ስድስተኛ አመቱን እያከበረ ነው።የሸገር የመጀመርያ ስርጭት የተጀመረው መስከረም 23/2000 ዓም ነው።
ሸገር -
- ማኅበራዊ ችግሮች የሚቀረፉበትን መንገድ በማመላከት፣
- ወቅታዊ መረጃዎችን በመስጠት እና
- የተዋጣለት ሀገርኛ ዘይቤ የተላበሱ መዝናኛ ፕሮግራሞቹን ለሕዝብ በማድረስ የቀዳሚነቱን ስፍራ እንደያዘ ብዙዎች የሚያወሱለት ነው።
ሸገር -
 - ለአዲሱ ትውልድ ጠንክሮ የመስራት ውጤትን አበክሮ በመንገር፣
 - ኢንዱስትሪያዊ ሰላም እንዲሰፍን ቀድሞ መረጃዎችን ለሚመለከታቸው ሁሉ በመስጠት፣
 - ያለፈውን በእርጋታ የመመልከት እና መጪውን ተስፋ በማመላከት በኩል ሸገር የተዋጣለት ነው።

ይህ ብቻ አይደለም ሸገር ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር! ብሎ መርሃግብሩን የሚጀምር እና የሚጨርስ ብቸኛ ሀገርቤትኛ የመገናኛ ብዙሃንም ነው።

ድምፀ መረዋዋ መዓዛ ብሩ የተዋጣለት የጋዜጠኝነትን ሙያ፣ስነ-ምግባር እና ኃላፊነት ያሳየች የሸገር 102.1 ራድዮ መስራች ነች።

ሸገሮች መልካም ልደት ሊባሉ ይገባል።
የሸገር ድህረ-ገፅ የፊት ገፅ ለመክፈት ይህንን ይጫኑ  - http://www.shegerfm.com

1 comment:

Anonymous said...

sew yehonech sew!!!!!

የክፍለዘመናችን የኢትዮጵያ የስልጣኔ ማማ መለኪያ የሆነው ታላቁ የኢትዮጵያ ጉባዔ ነገ በአዲስ አበባ ይከፈታል። ህልውናችን፣መጪው ስልጣኔያችን፣ሰላማችን እና ዕድገታችን በእዚህ ጉባዔ ውጤትና ሒደት ይወሰናል።

Foto : Fana digital  የቻልን በሀሳብ እና በጸሎት፣ ያልገባን እና የተምታታብን ደግሞ እኪገባን በዝምታ በመቆየት ኢትዮጵያን እናግዛት። ========= ጉዳያችን ልዩ ========= ኢትዮጵያ ሐምሌ 8፣2018 ዓም...