Thursday, October 3, 2013

ሸገሮች መልካም ልደት! ሊባሉ ይገባል



ሸገር ራድዮ ስርጭት የጀመረበት ስድስተኛ አመቱን እያከበረ ነው።የሸገር የመጀመርያ ስርጭት የተጀመረው መስከረም 23/2000 ዓም ነው።
ሸገር -
- ማኅበራዊ ችግሮች የሚቀረፉበትን መንገድ በማመላከት፣
- ወቅታዊ መረጃዎችን በመስጠት እና
- የተዋጣለት ሀገርኛ ዘይቤ የተላበሱ መዝናኛ ፕሮግራሞቹን ለሕዝብ በማድረስ የቀዳሚነቱን ስፍራ እንደያዘ ብዙዎች የሚያወሱለት ነው።
ሸገር -
 - ለአዲሱ ትውልድ ጠንክሮ የመስራት ውጤትን አበክሮ በመንገር፣
 - ኢንዱስትሪያዊ ሰላም እንዲሰፍን ቀድሞ መረጃዎችን ለሚመለከታቸው ሁሉ በመስጠት፣
 - ያለፈውን በእርጋታ የመመልከት እና መጪውን ተስፋ በማመላከት በኩል ሸገር የተዋጣለት ነው።

ይህ ብቻ አይደለም ሸገር ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር! ብሎ መርሃግብሩን የሚጀምር እና የሚጨርስ ብቸኛ ሀገርቤትኛ የመገናኛ ብዙሃንም ነው።

ድምፀ መረዋዋ መዓዛ ብሩ የተዋጣለት የጋዜጠኝነትን ሙያ፣ስነ-ምግባር እና ኃላፊነት ያሳየች የሸገር 102.1 ራድዮ መስራች ነች።

ሸገሮች መልካም ልደት ሊባሉ ይገባል።
የሸገር ድህረ-ገፅ የፊት ገፅ ለመክፈት ይህንን ይጫኑ  - http://www.shegerfm.com

1 comment:

Anonymous said...

sew yehonech sew!!!!!

የኢትዮጵያ ወቅታዊ ፖለቲካ፣ የአፈጀው የአዛውንቶች ክበብ፣ ''ፅንዶ'' እና ቅምጥሎቹ ''ባንዳ'' ዩቱበሮች በአውሮፓና አሜሪካ።

+++++++++++++ ጉዳያችን ወቅታዊ ምጥን +++++++++++++ መንደርደርያ ኢትዮጵያ በዘመን አቆጣጠሯ ስንሔድ የሐያ አንደኛውን ክ/ዘመን የመዠመርያ ሩብ ክፍለዘመን ለማጠናቀቅ ሰባት ዓመታት ብቻ ቀርተዋታል። ያለፈው ሐ...