Sunday, October 13, 2013

የአርሴናል ተጫዋች ኢትዮጵያዊው ጌድዮን ስለ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ጫወታ ምን አለ?


ጌድዮን

ለአርሴናል የሚጫወተው ጌድዮን የዛሬውን ጫወታ ከመጀመሩ በፊት በ ፌስቡክ ገፁ ላይ '' for #Ethiopian Nationla team: Good luck boys. I know you can do it '' (ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋቾች መልካም ዕድል! ጫወታውን  በሚገባ እንደምታሸንፉ አውቃለሁ) ነበር ያለው።ጫወታው ካለቀ በኃላ ''እኔ በጫወታ ችሎታ (በቡድናችን) እረክቻለሁ'' ነው ያለው። ጥሩ አባባል ነው።

በነገራችን ላይ ከዛሬው በኢትዮጵያ እና  በናይጄርያ መካከል የነበረው ጫወታ የምንረዳው  ዋልያዎች ናይጄርያን የማስጨነቅ አቅም እንዳላቸው ነው።
እድላችን ጠበበ እንጂ አሁንም በበቂ ዝግጅት በቀጣዩ ጫወታ የማሸነፍ ዕድላችን አልተዘጋም።ናይጄርያ ተዝናንተን (ሰፊ ዕድል ይዘን) ከመሄድ ተጠናቀን ለመሄድ የሚያስገድደን ነው።ተጨንቀን ናይጄርያ ላይ ካሸነፍን ድሉ ይብሱን ይጥማል።
በሩ አሁንም ሙሉ በሙሉ አልተዘጋም።
Getachew Bekele
oslo


No comments:

7ኛው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ግንቦት 24፣2018 ዓም በከፍተኛ የሕዝብ ተሳትፎ ተጠናቋል።

ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ በሰባተኛው ብሔራዊ ምርጫ ድምፅ ሲሰጡ። ስለምርጫው ዝርዝር ጉዳይ ምን ያውቃሉ? ✓ ሰባተኛው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ 42 ፓርቲዎች እና 73 የግል ተወዳዳሪዎች ለተለያዩ ምክር ቤቶች ዕጩዎች ...