ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Tuesday, October 29, 2013

የደቡብ ሱዳን ግዛት የአብዬ ህዝበ ውሳኔ የአፍሪካ ቀንድ አካባቢ ትኩሳትን እያጋለው ነው።


ጉዳያችን ጡመራ ጥቅምት 19/2006 ዓም
አብዬ ክልል በደቡብ እና ሰሜን ሱዳን መካከል የምትገኝ የሁለቱ ሃገራት አጨቃጫቂ ግዛት ነች።የ10,546 ስኩዌር ኪሎ ሜትር ስፋት ያላት አብዬ በነዳጅ ሃብቷ ከእሩቅ እስከ ቅርብ ያሉ ማላዮችን አይን ስባለች።የምዕራቡ ዓለምም ሆነ የአካባቢው ሃገራት ጉዳዩን ከሚገባው በላይ እንዲጮህ ያደረጉት የሰብአዊ መብት ጉዳይ ብቻ ቢሆን በጣም ደስ ይል ነበር። ግን ጉዳዩ ከሃብት ጋር መያያዙ እና ይህ ሃብት በሰሜን ሱዳን እጅ ከገባ የሚኖረው የኃይል ሚዛን ሃያላኑንም ሆነ የቅርብ ቡና አጣጪ ጎረቤቶችን ቀልብ ስቧል።

በአብዬ ግዛት አረብኛ እና እንግሊዝኛ ይነገራል።የተባበሩት መንግሥታት በግዛቲቱ ላለው ግጭት ሰላም አስከባሪ  ኃይል የሲቪልያንን ሕይወት እንዲታደጉ 4,200  የኢትዮጵያ ወታደሮች እንዲመደቡ ማድረጉ ይታወቃል።

ትናንት ጥቅምት 18/2006 ዓም ታዲያ ግዛቲቱ ወደ ሰሜን ወይንም ወደ ደቡብ ሱዳን ለመቀላልቀል የሕዝበ ውሳኔ አድርጋለች።ህዝበ ውሳኔውን የተባበሩት መንግሥታት እውቅና አልሰጠውም።ሆኖም ግን የውጭ ኃይላት የሉበትም ለማለት አይስደፍርም።
ዛሬ አልጀዚራ ''ኢንሳይድ ስቶሪ'' ፕሮግራሙ ''የአብዬ ህዝበ ውሳኔ ለሰላም ስጋት ነውን?'' በሚል አርዕስት ስር ያቀረበውን ውይይት ይመልከቱ።





ጉዳያችን GUDAYACHNgetachewb221@gmail.com

No comments:

ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።