ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Friday, October 11, 2013

''የቡርቃ ዝምታ'' ስለተሰኘው መፅሐፍ ከአስር ዓመት በላይ ስፈልግለት የነበረውን ስም ዛሬ አገኘሁት


''የቡርቃ ዝምታ'' የተሰኘውን መፅሐፍ ያነበብኩት ካልተሳሳትኩ የዛሬ አስራ አንድ ዓመት ገደማ ካምፓላ፣ዑጋንዳ ማካሬሬ  ዩንቨርስቲ ሳለሁ ነበር።መፅሐፉን አንብቤ እንደጨረስኩ የፀሃፊውን አላማ፣ስሜቱን እና ግቡን በደንብ ተረዳሁበት።ያለኝንም ሃሳብ ገፅ በገፅ ከሂስ ጋር ወደ ስድስት ገፅ ፅፌ መፅሐፉን ላዋሱኝ ሰው ሰጥቻቸው እንደነበርም ትዝ ይለኛል።.........

.......አንዳንድ ሰው ጥሩ የስነፅሁፍ ችሎታ (የአፃፃፍ ስልት) ሊኖረው ይችላል።ይህ ማለት ግን የተፃፈው ትክክል ነው ማለት አይደለም።ቆንጆ መልክ ያለው ሁሉ አመለ ሸጋ እንዳልሆነ ሁሉ። ጨካኙ ሂትለር ጥሩ ንግግር ሊናገር ይችላል።የንግግር አዋቂነቱ ግን የሚለውን ትክክለኛነት አይገልፅም።አንድ ሰው በጥሩ ንግግር ሃይማኖት ሊያስተምር ይችላል።ጥሩ በመናገሩ ግን የሚለውን ሁሉ የሃይማኖቱ አስተምሮ ከሚለው ጋር ሳላገናዝብ እንድቀበል አያደርገኝም።

ዛሬ የፌስ ቡኬን ገፅ ሳገላብጥ አንድ  ወዳጄ ከላይ ስለጠቀስኩት መፅሐፍ የሰጠው ስም ለአስር አመታት ስፈልግለት የነበረውን ስም ያገኘልኝ መሰለኝ። ወዳጄ ያለው '' የብልቃጥ ውስጥ መርዝ ሆነብኝ'' ነበር።ወዳጄን እንዳመሰግነው ይፈቀድልኝ።የብልቃጥ ውስጥ መርዝ የሚፅፉቱ እና የሚያፅፉቱ ብልቃጡን ማን እንደሚጨልጠው አይታወቅምና እባካችሁ ህዝብን ከህዝብ ጋር ለማጋጨት አትትጉ።


አበቃሁ
ጌታቸው በቀለ
ኦስሎ

No comments:

መንግስት ከዲፕሎማሲያዊ መፋዘዝ ይውጣ! የአረብ ሊግ በአባይ ግድብ አንጻር የወሰነውን የጸብጫሪነት ተግባር በውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር የምላሽ መግለጫ ብቻ የሚበቃ ሊሆን አይገባም።መንግስት ያልሰራው ግዙፍ ስራ ኢትዮጵያን ለአደጋ እንዳያጋልጣት ያሰጋል።

የኢትዮጵያ ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ዋና መስሪያቤት መንግስት በፍጥነት ሊሰራቸው የሚገቡት አምስት ወሳኝ ዲፕሎማሲያዊ ተግባራት ========= ጉዳያችን አለርት ========= የአረብሊግ አንዱ የሚታወቅበት መለያው እንደባዶ ቆር...