Friday, October 11, 2013

''የቡርቃ ዝምታ'' ስለተሰኘው መፅሐፍ ከአስር ዓመት በላይ ስፈልግለት የነበረውን ስም ዛሬ አገኘሁት


''የቡርቃ ዝምታ'' የተሰኘውን መፅሐፍ ያነበብኩት ካልተሳሳትኩ የዛሬ አስራ አንድ ዓመት ገደማ ካምፓላ፣ዑጋንዳ ማካሬሬ  ዩንቨርስቲ ሳለሁ ነበር።መፅሐፉን አንብቤ እንደጨረስኩ የፀሃፊውን አላማ፣ስሜቱን እና ግቡን በደንብ ተረዳሁበት።ያለኝንም ሃሳብ ገፅ በገፅ ከሂስ ጋር ወደ ስድስት ገፅ ፅፌ መፅሐፉን ላዋሱኝ ሰው ሰጥቻቸው እንደነበርም ትዝ ይለኛል።.........

.......አንዳንድ ሰው ጥሩ የስነፅሁፍ ችሎታ (የአፃፃፍ ስልት) ሊኖረው ይችላል።ይህ ማለት ግን የተፃፈው ትክክል ነው ማለት አይደለም።ቆንጆ መልክ ያለው ሁሉ አመለ ሸጋ እንዳልሆነ ሁሉ። ጨካኙ ሂትለር ጥሩ ንግግር ሊናገር ይችላል።የንግግር አዋቂነቱ ግን የሚለውን ትክክለኛነት አይገልፅም።አንድ ሰው በጥሩ ንግግር ሃይማኖት ሊያስተምር ይችላል።ጥሩ በመናገሩ ግን የሚለውን ሁሉ የሃይማኖቱ አስተምሮ ከሚለው ጋር ሳላገናዝብ እንድቀበል አያደርገኝም።

ዛሬ የፌስ ቡኬን ገፅ ሳገላብጥ አንድ  ወዳጄ ከላይ ስለጠቀስኩት መፅሐፍ የሰጠው ስም ለአስር አመታት ስፈልግለት የነበረውን ስም ያገኘልኝ መሰለኝ። ወዳጄ ያለው '' የብልቃጥ ውስጥ መርዝ ሆነብኝ'' ነበር።ወዳጄን እንዳመሰግነው ይፈቀድልኝ።የብልቃጥ ውስጥ መርዝ የሚፅፉቱ እና የሚያፅፉቱ ብልቃጡን ማን እንደሚጨልጠው አይታወቅምና እባካችሁ ህዝብን ከህዝብ ጋር ለማጋጨት አትትጉ።


አበቃሁ
ጌታቸው በቀለ
ኦስሎ

No comments:

በአቴንስ፣ግሪክ የምትገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን ላለፉት 40 ዓመታት በላይ ስትጠቀምበት የነበረውን ፖሊጎኖ የሚገኘው ቤተክርስቲያን በፖሊስ ታሸገ።የቅዱስ ሲኖዶስ አፋጣኝ ምላሽ እየተጠበቀ ነው።

የአቴንስ ኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን የታሸገችበት የጉግል የእንግሊዝኛ ትርጉም እና የግሪክኛ ዋናው ኮፒ። በግሪክ አቴንስ የምትገኘው እና ወደ ግማሽ ክ/ዘመን አገልግሎት ስትሰጥ የነበረችው እና በአቴንስ ፖሊጎኖ የምትገኘው የ...