Friday, October 11, 2013

''የቡርቃ ዝምታ'' ስለተሰኘው መፅሐፍ ከአስር ዓመት በላይ ስፈልግለት የነበረውን ስም ዛሬ አገኘሁት


''የቡርቃ ዝምታ'' የተሰኘውን መፅሐፍ ያነበብኩት ካልተሳሳትኩ የዛሬ አስራ አንድ ዓመት ገደማ ካምፓላ፣ዑጋንዳ ማካሬሬ  ዩንቨርስቲ ሳለሁ ነበር።መፅሐፉን አንብቤ እንደጨረስኩ የፀሃፊውን አላማ፣ስሜቱን እና ግቡን በደንብ ተረዳሁበት።ያለኝንም ሃሳብ ገፅ በገፅ ከሂስ ጋር ወደ ስድስት ገፅ ፅፌ መፅሐፉን ላዋሱኝ ሰው ሰጥቻቸው እንደነበርም ትዝ ይለኛል።.........

.......አንዳንድ ሰው ጥሩ የስነፅሁፍ ችሎታ (የአፃፃፍ ስልት) ሊኖረው ይችላል።ይህ ማለት ግን የተፃፈው ትክክል ነው ማለት አይደለም።ቆንጆ መልክ ያለው ሁሉ አመለ ሸጋ እንዳልሆነ ሁሉ። ጨካኙ ሂትለር ጥሩ ንግግር ሊናገር ይችላል።የንግግር አዋቂነቱ ግን የሚለውን ትክክለኛነት አይገልፅም።አንድ ሰው በጥሩ ንግግር ሃይማኖት ሊያስተምር ይችላል።ጥሩ በመናገሩ ግን የሚለውን ሁሉ የሃይማኖቱ አስተምሮ ከሚለው ጋር ሳላገናዝብ እንድቀበል አያደርገኝም።

ዛሬ የፌስ ቡኬን ገፅ ሳገላብጥ አንድ  ወዳጄ ከላይ ስለጠቀስኩት መፅሐፍ የሰጠው ስም ለአስር አመታት ስፈልግለት የነበረውን ስም ያገኘልኝ መሰለኝ። ወዳጄ ያለው '' የብልቃጥ ውስጥ መርዝ ሆነብኝ'' ነበር።ወዳጄን እንዳመሰግነው ይፈቀድልኝ።የብልቃጥ ውስጥ መርዝ የሚፅፉቱ እና የሚያፅፉቱ ብልቃጡን ማን እንደሚጨልጠው አይታወቅምና እባካችሁ ህዝብን ከህዝብ ጋር ለማጋጨት አትትጉ።


አበቃሁ
ጌታቸው በቀለ
ኦስሎ

No comments:

የክፍለዘመናችን የኢትዮጵያ የስልጣኔ ማማ መለኪያ የሆነው ታላቁ የኢትዮጵያ ጉባዔ ነገ በአዲስ አበባ ይከፈታል። ህልውናችን፣መጪው ስልጣኔያችን፣ሰላማችን እና ዕድገታችን በእዚህ ጉባዔ ውጤትና ሒደት ይወሰናል።

Foto : Fana digital  የቻልን በሀሳብ እና በጸሎት፣ ያልገባን እና የተምታታብን ደግሞ እኪገባን በዝምታ በመቆየት ኢትዮጵያን እናግዛት። ========= ጉዳያችን ልዩ ========= ኢትዮጵያ ሐምሌ 8፣2018 ዓም...