ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Tuesday, December 21, 2021

የአንድ ሚልዮን ኢትዮጵያውያን ጉዞ ወደ ሀገር ቤት በቡድን እየሆኑ የሚጎበኙት ቦታ ለማመቻቸት ከወዲሁ ከስር የተያያዘውን ፎርም እንዲሞሉ ጥሪ ቀርቧል።



በኢትዮጵያ ዘመናዊ ታሪክ የመጀመርያ የሆነው ኢትዮጵያ ልጆቿን ወደ ሀገር ቤት ኑ! የሚለው ጥሪ ከጠቅላይ ሚኒስቴር ዓቢይ እና ከቢሯቸው ከተላለፈ ገና አንድ ወር ቢሆነውም እስካሁን በመቶሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገር ቤት የገና በዓልን አስታከው ለመግባት ዝግጅት ላይ ናቸው።

በኢትዮጵያም ብሔራዊ ኮሚቴ መመስረቱ እና ከአዲስ አበባ ከተማ ጀምሮ ክልሎች ፈጣን ዝግጅት እያደርጉ ነው። የአሁኑ ጉዞ በተለይ ኢትዮጵያ በሽብርተኛው ህወሓት የደረሰባት የሽብር ጥፋት የፈረሰውን ለመገንባት፣የተሰበረውን ለመጠገን የሚደረግ ጉዞ ነው።በእዚህ መሰረት ወደ ኢትዮጵያ የሚሄዱ በቡድን በቡድን እየሆኑ ከስር የተለጠፈውን ማስፈንጠርያ (ሊንክ) በመጫን ፎርሙን እንዲሞሉ ማሳሰብያ ተሰጥቷል።በእዚህ መሰረት በሚዘጋጁት ጉብኝቶች መሳተፍ የሚችሉ ሲሆን ኢትዮጵያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ላልሰሙት መረጃውን እንዲያደርሱ ይጠየቃሉ።

በቡድን ሆነው የሚሞሉት ፎርም ሊንክ ከስር ተጭነው ከፍተው ከሞሉ በኃላ ''Submit'' የሚለውን ተጭነው ይላኩ።


========////========

No comments: