የተመድ ሰ/መ/ም/ቤት ስብሰባ ጀኔቫ ሲደረግ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አሕመድ ከቱርክ ፕሬዝዳንት ኤርጋዶን ጋር
ውይይት ላይ ነበሩ።የቱርክ አፍሪካ ጉባኤ ዛሬ በአንካራ ተከፍቷል።
ፎቶ = ታኅሳስ 8/2014 ዓም (ከጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ ትውተር ተወስዶ ለጉዳያችን እንዲሆን ሆኖ የቀረበ)
==============
ጉዳያችን ልዩ ሪፖርት
==============
በዛሬው ታህሳስ 8/2014 ዓም የተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ መብት ምክር ቤት ስብሰባ ላይ ንግግር ካደረጉት የሃገራት ተወካዮች ንግግር ውስጥ አብዛኞቹ ህገሮች በኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን እና በተመድ የሰብዓዊ መብት ካውንስል በጋራ የተደረገው ምርመራ አወድሰዋል።የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት መከበር እንዳለበት አስምረውበታል።
ከተናገሩት ውስጥ የ19ኙ ሃገሮች ያሉት ዋና ገዢ ሃሳቦች ከስር ቀርበዋል።ስብሰባው የተደረገው በጄኔቭ የተመድ ስብሰባ አዳራሽ ሆኖ ተናጋሪዎች በኮቪድ ወረርሽኝ ሳብያ በቀጥታ የቪድዮ ስርጭት ነበር የቀረቡት።ስብሰባው በሁለት ክፍል ከምሳ በፊት እና በኃላ የነበረው ስብሰባ በተመለከተ የተባለውን ከእዚህ በታች ቀርበዋል።
በክፍል አንድ ስብሰባ
በጧቱ ስብሰባ ላይ 19 ሀገሮች ተወካዮች ያሉት ዋና ጭብጦች የሚከተሉት ናቸው።



















ከእዚህ በተጨማሪ የተለያዩ ዓለም አቀፍ እና አካባቢያዊ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ተወካዮች አጫጭር ዕይታዎቻቸውን አካፍለዋል።
በክፍል ሁለት ስብሰባ
በክፍል ሁለት ማለትም ከምሳ በኃላ በነበረው ስብሰባ ላይ ድምጽ ከመሰጠቱ በፊት የምክር ቤቱ አባላት እና ኢትዮጵያ ሃሳብ እንድትሰጥ በተጠየቀው መሰረት የሚከተሉት ሀገሮች ይህንን ብለዋል።






በመጨረሻም የድምፅ መስጠቱ ስነስርዓት ተካሂዶ እንግሊዝ እና አሜሪካን ጨምሮ 21 ሀገሮች አዎን ሲመርጡ 15 ሀገሮች ቻይና እና ሩስያን ጨምሮ አይሆንም ብለዋል። የቀሩት 11 ሀገሮች ድምፀ ተአቅቦ አድርገዋል።
የስብሰባው አጠቃላይ አንደምታ እና መንግስት ማየት ያለበት መንገድ
በድምፅ ውጤቱ መሰረት የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብት ምክር ቤት ኤክስፐርቶች በመላክ ላለፈው አንድ ዓመት የነበረውን ሁኔታ አጥንቶ እንዲያቀርብ የሚል ሲሆን ኢትዮጵያ ውሳኔውን የቅኝ ግዛት አስተሳሰብ የተጠናወተው መሆኑን በመግለጫዋ አስታውቃለች።ሆኖም ግን አሁንም ኢትዮጵያ የህወሓት የሽብር ቡድንን በቶሎ ለሕግ አቅርባ እስከሄደች ድረስ እና ወደ ኢትዮጵያ የሚመጣውን ልዑክ ማንነት ( ውሳኔውን አልቀበልም ብላ ውድቅ ካላደረገችው) እስከመወሰን እና ቪዛ የምትሰጠው እና የማትሰጠውን እስከመወሰን ድረስ የራሷ ተግባር ነው። ሌላው የአፍሪካ ሀገሮችን አስተባብራ ዲፕሎማሲያዊ ግፊት አስደርጋ መልሳ ኮሚሽኑን በሂደት ስብሰባ አስቀምጣ ውሳኔውን ማስቀየር ትችላለች።
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን እና የተመድ ሰብዓዊ መብት ምክር ቤት በጋራ በትግራይ ያደረጉት ምርመራ የኢትዮጵያ መንግስት ሲቀበለው የሽብር ቡድኑ ህወሓት አልተቀበለውም።በመሆኑም አሁንም ምርመራው ይደረግ ቢባልም በህወሓት የተፈፀመው የሰብዓዊ መብት ጥሰት ፀሐይ የሞቀው ነው።እዚህ ላይ ማወቅ የሚገባው ግን የምዕራባውያን ፍላጎት ኢትዮጵያ ውስጥ ጉዳይ ገብቶ መፈትፈት እና በትግራይ ሕዝብ እና በተቀረው ሕዝብ መሃል ያለ ልዩነት በምርመራ ሂደት እያሰፉ በመጨረሻ ጉዳዩን ማወሳሰብ ነው።ስለሆነም የኢትዮጵያ መንግስት የዛሬውን ውሳኔ አስመልክቶ የሩቁ ግባቸውን ተመልክቶ ለትውልድ የሚጠቅም ብልህነት ያለው ውሳኔ መወሰን ይገባዋል።
ባጠቃላይ የዛሬው የውሳኔ ሂደት የሚያሳየው የተባበሩት መንግሥታት አባል ሀገሮች መሃል ያለው ልዩነት በግልጥ መስፋቱን እና ድርጅቱ ለውጥ ካላደረገ በቀር ውሳኔዎቹ ሁሉ የውሃ ላይ ኩበት እየሆኑ መሄዳቸው እንደማይቀር ነው።የዛሬው ውሳኔ ከሩስያ እና ቻይና በተጨማሪ ፊሊፒንስ እና ቬንዝዌላ ያሰሙት የምሬት ንግግር ከምዕራቡ ጋር የደረሰው ፍጥጫ የመጨረሻ ጫፍ እንደደረሰ በደንብ የሚያሳይ ነው። በእዚህ ጊዜ ኢትዮጵያ ውሳኔዎችን ባለመቀበል ለፍትህ መቆሟን በማሳየት የጀግና ጀግና ሆና በብዙ ሀገሮች አንጀት አርሳ እንደምትወጣ መመልከት ይቻላል።የመጨረሻው መጨረሻ ግን ኢትዮጵያውያን በሽብር ቡድኑ የተዋለባቸውን ግፍ በትግራይ ሕዝብ ላይ እንዳይፈፀም በጨዋነት በመንቀሳቀስ የሽብር ቡድኑን በፍጥነት መደምሰስ እና የትግራይ ህዝብንም ከመከራው አላቆ የህወሓትን ፕሮፓጋንዳ እና እኛኑ ለማጋጨት ያሰፈሰፉትን ባዕዳን አሳፍረን ችግራችንን ስንፈታ ሁሉም ያፍራል።
በዛሬው የተመድ ሰብዓዊ መብት ምክርቤት ስብሰባ ላይ ድምፅ የሰጡ የ47 ሀገሮች ዝርዝር እና የድምፃቸው ውጤት
No comments:
Post a Comment