ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Wednesday, July 1, 2020

ሰበር ዜና - ጀዋር መሐመድ፣በቀለ ገርባ እና ግብረ አበሮቹ በሰኞ ዕለቱ ግድያ ብቻ ሳይሆን ከእዚህ በፊት ባደረጉት ቅስቀሳ እና በጥቅምት ወር ለሞቱት 97 ሰዎች ወንጀል ሁሉ እንደሚከሰሱ የፌድራል ፖሊስ አስታወቀ

>> ከአሁን በኃላ ለሕግ ቀርበው በፍትህ እንጂ በሽምግልና የሚፈታ ምንም ነገር የለም - የፌድራል ፖሊስ 

የፌደራል ፖሊስ ዛሬ በኢትዮጵያ ቴሌቭዥን በኃላፊው በኩል በሰጠው መግለጫ የጀዋር መሐመድ ቡድን በአስከሬን ነጠቃ ብቻ አይደለም በፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋሉት ብሏል ፖሊስ በማብራርያው።ግለሰቦቹ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣኖችን በመግደል በአዲስ አበባ ላይ የሰኔ 15ቱ ዓይነት እልቂት ለመፈፀም ቀደም ብለው አቅደው እንደነበር ነው ከምርመራው ሂደት የተረዳነው እና እየወጡ ያሉት መረጃዎች ያለው የፖሊስ መግለጫ፣በእነ ጀዋር ላይ የሚደረገው ክስ በእዚህ ሳምንት ባደረጉት የመግደል ሙከራ ብቻ ሳይሆን ከእዚህ በፊት በተደጋጋሚ ሲቀሰቅሱ የነበሩበት ሂደት እና በጥቅምት ወር ላይ ባደረጉት ቅስቅሳ ለጠፋው የ97 ሰው ሞት ጭምር ጉዳዩ ተመርምሮ ለፍርድ እንደሚቀርቡ ዛሬ አዲስ አበባ ላይ በተሰጠው መግለጫ ለማወቅ ተችሏል።

የፖሊስ ኮሚሽነሩ መግለጫ በተለይ የእነጀዋርን ጉዳይ አስመልክተው ሲናገሩ ከአሁን በኃላ በሽምግልና ወይንም በሌላ መንገድ የሚታይ ምንም ዓይነት ዕድል አለመኖሩን እና ጉዳዩ በአስቸኩአይ አዋጅ ውስጥ ብንሆንም ለሕግ እና ስርዓት መከበር ምርመራው በሚገባ ተፈፅሞ ለፍርድ ይቀርባሉ ብለዋል።የምርመራውን ውጤትም በእየጊዜው ለሕዝብ እንደሚገለጥ ነው የፖሊስ ኮሚሽነሩ ያብራሩት።
 

"ደወል" በገጣሚት ረድኤት ተረፈ 

ከጦብያ ግጥምን በጃዝ የተወሰደ  

ግጥሙ ከላይ ከተፃፈው ዜና ጋር አይገናኝም 

 
 

No comments: