Monday, July 13, 2020

በኖርዌይ፣ ኦስሎ እና በዙርያዋ ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን፣ትውልደ ኢትዮጵያውያን እና የኢትዮጵያ ወዳጆች በሙሉ የቀረበ ጥሪ - ለትውልድ የምትቆይ ኢትዮጵያን ለማቆየት ሁለት ሰዓታትን ለኢትዮጵያ ከመመስከር ያነሰ አይደለም።

ኢትዮጵያ ዛሬ በስሜት ከቤቱ የሚናደድ፣የሚቆጭ እና እንዲህ ቢሆን እያለ የሚያወራ ሰው አይረባትም።ወቅቱ ቢያንስ ለሀገር በአደባባይ የመመስከር እና የጋራ ድምፅን የማሰምያ ጊዜም ነው።ወቅቱ በዓለም አደባባይ ''ኢትዮጵያ ትውደም'' (ዳውን ዳውን ኢትዮጵያ) እያሉ የሚሞላቀቁ 'የጉድ ትውልዶች' የታዩበትም ጊዜ ነው። 
በእዚህ ጊዜ ከቤተሰብ ጋር ወጥቶ ለኢትዮጵያ አለመመስከር ትልቅ ስህተት ነው።በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ከቤተሰብ እና ወዳጅ ዘመድ ጋር በከተማዎች ይመላለሳሉ።ከእዚህ ጊዜያቸው ውስጥ ሁለት ሰዓታት ለኢትዮጵያ እንዲመሰክሩ ለመጪው ረቡዕ ጁላይ 15/2020 ከ 14 እስከ 16 ሰዓት ባለው ጊዜው ውስጥ ኦስሎ የሚገኘው የኖርዌይ ፓርላማ Karl Johans gate 22 / 0026 Oslo በመገኘት ለኢትዮጵያ ድምፅ እንዲሆኑ ይጠየቃሉ።






No comments:

7ኛው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ግንቦት 24፣2018 ዓም በከፍተኛ የሕዝብ ተሳትፎ ተጠናቋል።

ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ በሰባተኛው ብሔራዊ ምርጫ ድምፅ ሲሰጡ። ስለምርጫው ዝርዝር ጉዳይ ምን ያውቃሉ? ✓ ሰባተኛው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ 42 ፓርቲዎች እና 73 የግል ተወዳዳሪዎች ለተለያዩ ምክር ቤቶች ዕጩዎች ...