ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Monday, July 13, 2020

በኖርዌይ፣ ኦስሎ እና በዙርያዋ ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን፣ትውልደ ኢትዮጵያውያን እና የኢትዮጵያ ወዳጆች በሙሉ የቀረበ ጥሪ - ለትውልድ የምትቆይ ኢትዮጵያን ለማቆየት ሁለት ሰዓታትን ለኢትዮጵያ ከመመስከር ያነሰ አይደለም።

ኢትዮጵያ ዛሬ በስሜት ከቤቱ የሚናደድ፣የሚቆጭ እና እንዲህ ቢሆን እያለ የሚያወራ ሰው አይረባትም።ወቅቱ ቢያንስ ለሀገር በአደባባይ የመመስከር እና የጋራ ድምፅን የማሰምያ ጊዜም ነው።ወቅቱ በዓለም አደባባይ ''ኢትዮጵያ ትውደም'' (ዳውን ዳውን ኢትዮጵያ) እያሉ የሚሞላቀቁ 'የጉድ ትውልዶች' የታዩበትም ጊዜ ነው። 
በእዚህ ጊዜ ከቤተሰብ ጋር ወጥቶ ለኢትዮጵያ አለመመስከር ትልቅ ስህተት ነው።በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ከቤተሰብ እና ወዳጅ ዘመድ ጋር በከተማዎች ይመላለሳሉ።ከእዚህ ጊዜያቸው ውስጥ ሁለት ሰዓታት ለኢትዮጵያ እንዲመሰክሩ ለመጪው ረቡዕ ጁላይ 15/2020 ከ 14 እስከ 16 ሰዓት ባለው ጊዜው ውስጥ ኦስሎ የሚገኘው የኖርዌይ ፓርላማ Karl Johans gate 22 / 0026 Oslo በመገኘት ለኢትዮጵያ ድምፅ እንዲሆኑ ይጠየቃሉ።






No comments:

የተወካዮች ምክርቤት (ፓርላማው) አሰራሩ እና ውሳኔ አሰጣጡ የ21ኛውን ክ/ዘመን የሚመጥን፣ ኢትዮጵያ የመጀመርያ ፓርላማዋን ከከፈተች ከ80 ዓመታት በላይ እንደሆናት በሚያሳይ ልክ አይደለም።

አሁን በአራት ኪሎ የሚገኘው የኢትዮጵያ ፓርላማ ህንጻ በ1928 ዓም  =========== ጉዳያችን ========== የኢትዮጵያ ህዝብ ተወካዮች ምክርቤት በድረገጹ ላይ የኢትዮጵያ ፓርላማ ታሪክ በሚለው ርዕሱ ስር እንዲህ የ...