ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Saturday, May 23, 2020

የክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መደመር የተሰኘው መፅሐፍ በድምፅ ቀርቦልዎታል።ያድምጡ!

የጉዳያችን ማስታወሻ
**************
ኢትዮጵያውያን በእየዘመናችን ለአገራቸው ብቻ ሳይሆን ለመላው ዓለም የሚተርፍ ዕውቀት፣ብልሃት እና አርቆ ማስተዋል የታደሉ ሰዎች ተነስተውላታል።በቅርብ ዘመን ብናነሳ ጠቅላይ ሚኒስትር አክሊሉ ሃብተወልድ እና ቀዳማዊ አፄ ኃይለስላሴን መጥቀስ ይቻላል።ሁለቱም አፍሪካን ጨምሮ በመላው ዓለም ዛሬም ድረስ የተከበሩ ናቸው።ሁለቱም መላ ዘመናቸውን ለኢትዮጵያ ሲሰሩ ቢኖሩም ሕይወታቸው ያለፈው ግን በኢትዮጵያውያን ነው።

ጠቅላይ ሚኒስትር  አክሊሉ ህዳር 14/1967 ዓም ከስልሳዎቹ ጋር በጥይት ተደብድበው ሞቱ።አፄ ኃይለስላሴም እንዲሁ በምስጢር ተገድለው 17 ዓመት ሙሉ ከቤተመንግስት ስር ተቀብረው ኖሩ።እኛ እንዲህም ነን።እራሳችንን በራሳችን እጃችንን የምንቆርጥ።ዛሬም በአፄ ምንሊክ ላይ የሚከራከር ትውልድ፣ አክሊሉ ሀብተወልድንም ሆነ ቀዳማዊ አፄ ኃይለስላሴን ቢያገኝ ከመስቀል የማይመለስ ትውልድ ተዋፅኦም ነን።ለኢትዮጵያ ዲሞክራሲ እና ሰላም ቤተሰባቸውን በትነው በረሃ የወረዱት አንዳርጋቸው ፅጌንና ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በአግባቡ ማክበር ያቃተው ትውልድ የቀደሙትን ከመስቀል የማይመለስ ነው።እኛ እንዲህም ነን።በእርግጥ ሁላችንም እንዲህ አይደለንም።ታሪካችን ላይ ግን እንዲህ ዓይነት ክፉ ታሪኮችም አሉብን።ቁምነገሩ ካለፈው ስህተት ዛሬ ምን ተማርን? ነው።

በዘመናችን ከተነሱት ነገን የሚመለከቱ ብቻ ሳይሆን በአጭር ጊዜ ዓለም ያደነቃቸው እና ከፍተኛውን የኖቤል ሽልማት ያጎናፀፋቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አሕመድ ለአንዳንዶች ዛሬም እንደቀደሙት ዕንቁዎቻችን ካለ በቂ ምክንያት ''በውሃ ቀጠነ'' ጉዳይ ሊያጣጥሉ ሲሞክሩ ያለፈው የታሪካችን ጠባሳ እንዳይደገም ብለው ለአፍታም ያህል እያሰቡ አይመስልም።እስኪ ቢያንስ በእዚህ ዘመን ያለን እንንቃ! ሃሳቦችን በመመርመር እና በመተቸት ላይ የተመሰረተ ስብዕና እናዳብር።
*************
የጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ መደመር መፅሐፍ በድምፅ ለመከታተል ወይንም ወደ ኮምፕዩተርዎ ወይንም ስልክዎ ለማውረድ (''ዳውንሎድ'' ለማድረግ) ይህንን ገፅ ይክፈቱ እና ያዳምጡ።
ገጹን ለመክፈት ይህንን ይጫኑ >> https://medemer.et/am/book/?fbclid=IwAR1VOjUk_2anOT8hP0L9nXAWMU0bzk6DqyrNswRLxQUAFiQ5bzLvynPc2XE

ጉዳያችን ሚድያ፣ኮሚኒኬሽን እና ምክር አገልግሎት 
Gudayachn Multimedia, Communication and Consultant
Gudayachn Multimedia, Kommunikasjon og Konsultent 

No comments:

ህወሓት ሰሜን ወሎ ራያን ወርሮ የገጠር ወረዳዎችን እየዘረፈ ነው። ህዝብ ሲዘረፍ እና በአስር ሺዎች ሲፈናቀሉ የመንግስት የፖለቲካም ሆነ የወታደራዊው አመራሮች ዝምታቸው ከተጠያቂነት አያድናቸውም።

በሰሞኑ የህወሓት ወረራ ቆቦ ተፈናቅለው የገቡ የሰሜን ወሎ ተፈናቃዮች  በከፊል ፎቶ፡ ቢቢሲ ሚያዝያ 20፣2024 እኤአ ''ቅጥ አምባሩ የጠፋው'' የፕሪቶርያው ውል   ''ስኩዌር ዋን&#...