ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Monday, May 4, 2020

የልጅ አዋቂው ጠቅላይ ሚንስትር ዓቢይ፣ ማስተዋል ያነሳቸውን አዛውንቶቹን የህወሓት ባለስልጣናት ለፍርድ ቢያቀርብ መቀሌ በከበሮ እንደምትደምቅ አትጠራጠሩ።


የጉዳያችን ማስታወሻ 
ሚያዝያ 27/2020 ዓም
  • በፅሁፉ መጨረሻ ላይ የቴዎድሮስ ካሕሳይ የትግሪኛ አዲስ ዜማ ቪድዮ ይመለከታሉ።

የልጅ አዋቂ የሚለው አባባል በኢትዮጵያውያን ብሂል ውስጥ የተለመደ ነው።ይህ ስም የሚሰጠው ሰው የግድ እድሜው በልጅ እድሜ ክልል የሚገኝ መሆን ኖሮበት አይደለም።ጎረምሳም ቢሆን ጎልማሳ ከአዛውንቶች ያነሰ ዕድሜ  ያለው ነገር ግን አስተሳሰቡ በሳል ከሆነ የልጅ አዋቂ የሚል ስያሜ ያገኛል።ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ ወደ ስልጣን ከመጡ ጀምሮ በርካታ ተግባራት ተከናውነዋል።የለውጡ ሂደት በራሱ በብዙ የስልጣን ፍላጎቶች፣የጥቅም ውጥረቶች፣የጎሳ ስሜቶች እና የአካባቢው ጅኦ-ፖለቲካ ሹክቻዎች ብታዩበትም ኢትዮጵያን እንደአገር ከማስቀጠል አልፎ በዓለም አቀፍም ሆነ በአካባቢያዊ ፖለቲካዊ እና ምጣኔ ሃብታዊ ቦታ አስፈላጊ አገር የመሆኗ ዕውነታ እንደገና ጎልቶ እንዲታይ አድርጎታል።

በእነኝህ ሁሉ ሂደቶች ውስጥ ግን የህወሓት ግልጥ እና ስውር ተንኮል በኢትዮጵያ ፖለቲካም ላይ ሆነ በምጣኔ ሃብቷ እና በውስጥ ሰላም እንዲሁም በሕዝብ የእርስ በርስ ግንኙነት ሁሉ ላይ ከፍተኛ ጉዳት  አድርሷል።የህወሓት የደህንነት ባለስልጣናት አቶ ጌታቸው አሰፋን ጨምሮ ወደ መቀሌ እና ውጪ አገራት ከመሸሻቸው በፊት በኢትዮጵያ ያሉ ስስ የሆኑ የሃይማኖት ውጥረቶች፣የብሔር ቁርሾዎች እና የጥቅም ግጭቶች ያበጡባቸውን ቦታዎች ያውቁ ስለነበር እነኝህን ሁሉ አንድ በአንድ እየቆሰቆሱ እና በገንዘብ እንዲሁም በሰው ኃይል ድጋፍ እየሰጡ ግጭቶች በየቦታው እንዲፈነዱ አድርገዋል።ለግጭቶቹ ሁሉ ህወሓት ብቻ ተጠያቂ ነው ባይባልም በቀጥታ የለሉበትን ግጭቶች ግን ባብዛኛው በሎጀስቲክ፣በምክር እና በአይዞህ ባይ ፕሮፓጋንዳ የህወሓት ባለስልጣኖች እንደተባበሩ እና የይሁንታ ምልክት ሲያሳዩ እንደነበር የአደባባይ ምስጢር ነው።

ህወሓት በእነኝህ ግጭቶች ሁሉ አልሳካ ሲላት በምጣኔ ሃብት ሴራ ውስጥ በቻለችው ለመነከር ሞከረች፣ይህ የምጣኔ ሃብቱ ሴራ አገር ያሽመደምዳል በመቀጠል ወደ ፖለቲካዊ ቅራኔ ያድጋል ብለው ሲያስቡ የኮሮና ወረርሽኝ መጥቶ ምጣኔ ሃብቱ ወደ የአደጋ ዕዝ  ባህሪ መያዙ ሲታወቅ እና የተማመኑበት የገንዘብ አቅምም በራሱ በቀውሱ ምክንያት እንደሚሟ ሲያውቁ ሁኔታዎች አለማዋጣታቸው ግልጥ ሆነላቸው።

ይህ በእንዲህ እያለ ነበር ህወሓት በኮረና ወረርሽኝ ሳብያ የዓለም ትኩረት በመቀየሩ በአለን አቅም የአቶ ኢሳያስን መንግስት መቀየር ላይ ብንሰራ የተሻለ ነው ወደሚለው ቀድሞም ያሰቡት ግን በሁለተኛ ደረጃ ሊሰራ ያቀዱትን ሥራ በቀዳሚነት የመስራት ውሳኔ ላይ የደረሱት። ይህ በእንዲህ እያለ ደግሞ የዓባይ ጉዳይ ከግብፅ ጋር ውዝግቡ ሲባባስ ህወሓት አዲስ አጀንዳ በውስጥ ማራመድ ጀመረች።በእዚህ ጊዜው ውስጥ ትኩስ የሆነ የነገር መጫርያ አጀንዳ ባልነበረበት ወቅት የህወሓት ባለስልጣናት ትኩስ ነገር መጫርያ አጀንዳ ሲያፈላልጉ የምርጫ ቦርድ በኮሮና ምክንያት የምርጫው ጊዜ ሰሌዳ በታሰበው ጊዜ ሊደረግ እንደማይችል ገለጠ። ይህ ጥሩ አጀንዳ ሊሆን እንደሚችል የህወሓት ባለስልጣናት ገመቱ። ስለሆነም ምርጫው መደረግ አለበት፣ካልሆነ ግን ትግራይ በራሷ ምርጫ ታደርጋለች የሚል ውሳኔ የማዕከላዊው የህወሓት ኮሚቴ ወሰነ ሲሉ ሚያዝያ 26/2012 ዓም ምሽት አስነገሩ።

ህወሓት በትግራይ ምርጫ ቢያደርግ ባያደርግ ለህልውናው ይረዳዋል? ብለን ብንጠይቅ እንደ ትግራይ ክልል ምንም ለውጥ አያመጣም። ድርጅቱ አፋኝ እና አምባገነን ለመሆኑ የትግራይ ሕዝብ ከማንም የበለጠ ያውቀዋል።ምርጫውም ለይስሙላ እንደሚሆን ፀሐይ የሞቀው ነው። ህወሓት ሕጋዊ አድርጎ እራሱን ለማታለል ብቻ የሚጠቀምበት ምርጫ እንደሆነ አላፊ አግዳሚው የሚያውቀው ነው። ይልቁንም የትግራይ ሕዝብ ወደ ኤርትራ የሚወስደው መንገድ የሚከፈተው እና ሕዝብ እንደፈለገ ነግዶ እና ገዝቶ የሚኖረው  ህወሓት ከስልጣኑ ሲወገድ  እንደሆነ ያውቃል።ይህ ብቻ አይደለም በትግራይ የኑሮ ውድነቱ ዋነኛ  ምክንያት በአቦይ ስብሐት እና ቤተሰባቸው በመላዋ ትግራይ የተዘረጋው የቤተሰብ የንግድ መረብ እንደሆነ ያውቃል።ከእዚህ በተጨማሪም ህወሓት ከአሁን በኃላ ለማዕከላዊ መንግስት ያለመታዘዝ ተግባሩን ከጨመረ ከማዕከላዊ መንግስት ከበጀት ጀመሮ  እስከ መሰረታዊ ፍጆታዎች ድረስ ህዝቡ ላይ የሚደርሰው ተጨማሪ የኑሮ ውድነት ከባድ እንደሚሆን ሁሉም የሚረዳው ነው።

ይህ ሁሉ ሲሆን ግን በልጅ አዋቂው ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ በኩል የታየው ትዕግስት፣አርቆ ማስተዋል እና አላስፈላጊ የቃላት ምልልስ ውስጥ ከመግባት ይልቅ የመንግስት የዕለት ከዕለት ሥራ ላይ ማትኮሩ ለራሱ ለትግራይ ሕዝብ እና አዛውንቶች ግርምታን እና አድናቆትን አትርፏል።በተለይ በለውጡ መጀመርያ አካባቢ ህወሓት የትግራይ ተወላጆች በሙሉ ሊታሰሩ ነው፣ነግደው መኖር አይችሉም፣እያለች እርሷ እንደሸሸችው የትግራይ ሕዝብ በሙሉ መቀሌ እንዲገባ በውስጥም በግልጥም ያደረገችው ቅስቀሳ ሁሉ ውሎ አድሮ ውሸት መሆኑ ሲታወቅ ህወሓት ክፉኛ በትግራይ ሕዝብ እንድትጠላ ሆናለች።ይህንን አባባል አንዳንዶች ውሸት አድርገው ያዩታል።ይህንን የሚሉት በተለይ በውጭ  አገር ያሉ ካድሬ በመሆናቸው በኤርትራ ስደተኞች ስም የመጡ ከህወሓት የበለጡ ህወሓቶች በማኅበራዊ ሚድያ የሚሉት መሬት ላይ ያለውን የትግራይ ሕዝብ ስሜት የሚገልጥ አይደለም።

ስለሆነም ህወሓት አሁን የመጨረሻው መጨረሻ ላይ ደርሳለች።አጀንዳዎቿ ሁሉ አልቀዋል።የግጭት ፖለቲካዋ ከጎሳ እስከ የሃይማኖት ግጭት የሞከረችው ከሸፈ።ዛሬ ኢትዮጵያ ብዙ ስራዎች ቢያስፈልጉትም ከክልል የፖለቲካ ስሞች ከተከፋፈለ ኢህአዴግ ወደ ብልጥግና በሚል የሱማሌ እና የአፋር ክልል ሳይቀሩ የፖሊሲ አውጪነቱ ኃላፊነት ደርሰዋል።ይህ ብዙ ሥራ የሚፈልግ ቢሆንም ከአደገኛ የመበታተን አደጋ ቢያንስ በመዋቅር አያያዝ የተሻለ ማዕቀፍ ተፈጥሯል። የልጅ አዋቂው ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ በሚገባም በማይገባ መንገድ የሚተቹት የመኖራቸውን ያህል ወደኃላ ሂደቱን ስንመለከት ግን ብዙዎቹ ሂደቶች ትዕግስት  እና ማስተዋል የተሞሉ ነበሩ።አሁን ህወሓት በደረሰበት ምርጫ ለብቻዬ አደርጋለሁ የሚለው አደገኛ የቀይ መስመር ማለፍ ሂደት ግን የልጅ አዋቂው በቀላሉ ያልፈዋል ወይ? የሚለው አጀንዳ የሰሞኑ አጀንዳ መሆኑ አይቀርም።

አጀንዳው ከመወያያ አልፎ ሕጋዊ መሰረት የሌለው እና ህገ መንግስ ይከበር እያለ በመናገር የሚቀድመው የሌለው ህወሓት አሁን እራሱ የሕገ መንግስቱ ዋነኛ ጠላት መሆኑን መቀሌ ከገባ በኃላም አረጋግጧል።የአሁን ህገ መንግስቱን መጣስ ግን የልጅ አዋቂውን የመጨረሻ ደወል እንዲያሰማ የሚያስገድድ እንዳይሆን ያሰጋል።በእዚህ በኮሮና ዘመን ዓለም ሁሉ  ትኩረቱ ወረርሽኙ ላይ ነው።የኢትዮጵያ አየር ኃይል መቀሌ ገብቶ በወንጀል ሲፈለጉ የነበሩትን በቁጥጥር ስር አዋለ የሚለውን ዜና ዓለም በዜና አርእስት  ደረጃም አያነበው።ምክንያቱም ዜናው ሁሉ ኮሮና ነው።ይህ በራሱ ለልጅ አዋቂው መልካም አጋጣሚ ይፈጥራል።በሌላ በኩል የልጅ አዋቂው ዝም ብሎ ወደ እዚህኛው እርምጃ አይገባም።መጀመርያ የትግራይ ሕዝብ በራሱ በህወሓት ላይ የሚነሳበት ብዙ ምክንያቶች በአጀንዳ ላይ ተቀምጠዋል።አጀንዳዎቹ ደግሞ የልጅ አዋቂው ብቻውን አይመክርባቸውም። የአስመራው ፕሬዝዳንት (በአራዳ አነጋገር ''ኢሱ'') በትግራይ የሚፈጠረው ቀውስ ያሳስባቸዋል።

ህወሓት ከመቀሌ ቢወገድ የሚኖረው ክፍተት የህዝብ ስደት እንዳያስከትል እና ግጭት እንዲፈጠር ኢሱ የማይፈልጉበት ሁለት ምክንያቶች አሉ።የመጀመርያው ሌላ በግርግሩ ስሙን የቀየረ ህወሓት እንዳይመጣ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ በሚኖረው አለመረጋጋት መዘዙ ለራሷ ለአስመራም ስለሚተርፍ ነው።ስለሆነም በእዚህ ሳምንት መጨረሻ አዲስ አበባ ደርሰው ሰኞ ምሽት አዲስ አበባን የለቀቁት አቶ ኢሳያስ ዋና አጀንዳቸው ህወሓት እና ህወሓት እንደሚሆን አለመገመት አይቻልም። የሆነው ሆኖ ግን  የልጅ አዋቂው  ጠቅላይ ሚንስትር ዓቢይ፣ ማስተዋል ያነሳቸውን አዛውንቶቹን የህወሓት ባለስልጣናት ለፍርድ ቢያቀርብ መቀሌ በከበሮ እንደምትደምቅ አትጠራጠሩ።

አዲሱ የቴዎድሮስ ካሕሳይ የትግሪኛ ዜማ 




ጉዳያችን GUDAYACHN
 www.gudayachn.com

No comments:

ህወሓት ሰሜን ወሎ ራያን ወርሮ የገጠር ወረዳዎችን እየዘረፈ ነው። ህዝብ ሲዘረፍ እና በአስር ሺዎች ሲፈናቀሉ የመንግስት የፖለቲካም ሆነ የወታደራዊው አመራሮች ዝምታቸው ከተጠያቂነት አያድናቸውም።

በሰሞኑ የህወሓት ወረራ ቆቦ ተፈናቅለው የገቡ የሰሜን ወሎ ተፈናቃዮች  በከፊል ፎቶ፡ ቢቢሲ ሚያዝያ 20፣2024 እኤአ ''ቅጥ አምባሩ የጠፋው'' የፕሪቶርያው ውል   ''ስኩዌር ዋን&#...