Wednesday, November 2, 2016

ጥቅምት 23 የታሪካችን አካል (ቪድዮ)

ዛሬ ጥቅምት 23 ነው።እስካሁን አንድም ሐውልት ያልቆመላቸው ቀዳማዊ አፄ ኃይለ ስላሴ የነገሱት የዛሬ 86 ዓመት ጥቅምት 23/1923 ዓም በአሁኑ አራዳ (ፒያሳ) የሚገኘው ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ነበር።ሃውልት ብቻ አይደለም በስማቸው የተሰየመውን ከዩንቨርሲቲ እስከ የካቲት 12 ሆስፒታል ስም እየደለዝን የእራሳችንን ታሪክ ለመፃፍ የሞከርን ጉደኞች አሁንም እኛው ነን።
ይህም የታሪካችን አካል ነው።

ንግስት መነን የመጀመርያ የልጃገረዶች ትምህርት ቤት መስራች፣የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል እና በኢየሩሳሌም ያሉ ገዳማት ያደርጉት አስተዋፅኦ ሁሉ የሚጠቀስ ታሪክ ነበራቸው።ከሁሉም የኢትዮጵያ ሴቶችን ንግስት መነን እኩልነትን ለማጠናከር የለፉ ነበሩ።ስለ ዓለም የሴቶች እኩልነት እናወራለን እንጂ የእኛዎቹን ፈላስፋዎች ማድነቅ አልፈጠረብንም።አንድ ቀን ይህንን ሁሉ ምስቅልቅል የሚያስተካክል እና ወደ እራሳችን ሀብት የሚመለከት ትውልድ ይነሳል።እስከዛው ድረስ ግን ለማያውቀው  ጠብታ ተጠራቅሞ ጋን ይሞላል እና እንዲህ የጠብታ ያህል እንነግራለን።



ጉዳያችን GUDAYACHN www.gudayachn.com

No comments:

''ሙዝ አትብላ! ጦጣዎች ከጫካ ሊመጡ ይችላሉ።'' ዓይነቱ የጀዋር ጊዜው ያለፈበት ትንተና በኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ላይ።

ቀይ ባሕር ዛሬ በዩቱብ አገኘን ብላችሁ በኢትዮጵያ የባሕር በር ጉዳይ ላይ የምትሳለቁ የዘመናችን ባንዳዎች ግዴላችሁም ጊዜ እና ትውልድ ይፈርዳል! እናንተን ብቻ ሳይሆን ልጆቻችሁም ''አባታቸው በዩቱብ ኢትዮጵያ ...