ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Thursday, November 17, 2016

በኦስሎ በወቅታዊ የሀገራችን ተያያዥ ጉዳዮች ዙርያ ልዩ ውይይት በኢትዮጵያውያን የጋራ መድረክ ኖርዌይ ተዘጋጀ

ካልተወያዩ ኢትዮጵያን በምኞት አይገነቧትም።ሃሳባችንን እናካፍል!
የሌሎችንም ሃሳብ እንስማ !

ተወያዩ! ዝም አትበሉ።የሀገራችን ጉዳይ ያገባናል።ሁላችንም ሃሳቦች አሉን።ሃሳቦቻችንን ለሌሎች ማካፈል ካልቻልን ወይንም የሌሎች ሃሳቦችን መስማት ካልቻልን ነገ ምን አይነት ኢትዮጵያ እንድትኖረን እንፈልጋለን? ኢትዮጵያን በምኞት መገንባት አይቻልም ሃሳቦችን በማንሸራሸር የጋራ ግንዛቤ በመያዝ ግን አንድ እርምጃ ወደፊት መሄድ ይቻላል።

 የትግራይ ነፃ ኣውጭ ግንባር (ሕወሓት) ወደ ኋላ በመጓዝ በዘመነ ደደቢት ላይ ይገኛል::ኢትዮጵያ ሙሉ በሙሉ በህዋሃት መኮንኖች ስር ወድቃለች::ማሰር መግደል እያንዳንዱ መኮነን መብት ብቻ ሳይሆን የኣንድ ተራ ወታደርና ፖሊስ መብት ሆኗል:: በአንድ ወር ብቻ እስከ መቶ ሺህ የሚገመቱ ኢትዮጵያዊያን ወደ ስር ተግዘዋል::በዘመነ ደደቢት ጊዜ እስር ቤቶች የተፈጥሮ ዋሻዎችና ሰው ሰራሽ ጉድጓዶች በነበሩበት ወቅት የእስር ቤቶች ኣዛዦች የነበሩት ኣሁንም መርማሪዎች የእስር ቤቶች ኣለቆች ናቸው:: በኢትዮጵያ ታሪክ ያልታየ እስር ቤቶችን በ እስርኞች እንደተሞሉ ማቃጠል ኢትዮጵያ ውስጥ የተለመደ ሆኗል::

ታዲያ በደረስንበት በዘመነ የተቋሚዎች ኣሰላለፍ ምን ይመስላል?
በተለይ በነፃ የመደራጀት እድል ያላቸው በውጭ ኣገር የሚገኙ ተቃዋሚዎች ኣሰላለፍ ምን ይመስላል?
በጣም ሊበረታታ የሚገበው በብሔራዊ ደረጃ ወይም በኣገር ኣቀፍ የተደራጁ ኣሉ
በርካታ ድርጅቶች በብሄራቸው ተደረጅተው የሚታገሉ ኣሉ::  የኦሮሞ ህዝብ በብሔር ተደራጅቷል::  ኣማራም  በብሔር መደራጀት ጀምሯል::

በኣደረጃጀት ዙሪያ በርካታ ጠንክር ጠንከር ያሉ መተቻቸቶች ይታያሉ::ትችቶች ገንቢ ናቸው?
የተቀዋሚው ኣደረጃጀት በቂ ነው?
ራሳቸውንና ህዝቡን ለመከላከል በጎበዝ ኣለቃ ተደራጅተው እየታገሉ እንዳሉ እየተሰማ ነው።በቂ ትኩረትና ድጋፍ ኣግኝተዋል?  ካላገኙ ለምን? ሕዝብ በውጭ እና በአገር ቤት ያለው ምን እያደረገ ነው?

እነኝህን እና ተያያዥ ወቅታዊ የሀገራችን ጉዳዮች ዙርያ የኢትዮጵያውያን የጋራ መድረክ በኖርዌይ በመጪው ቅዳሜ የጠረንጴዛ ዙርያ ውይይት አዘጋጅቷል።ውይይቱ በቪድዮ የሚዘጋጅ ሲሆን በውይይቱ ላይ ለመሳተፍ የሚፈልግ ማንኛውም የኢትዮጵያ ጉዳይ ይመለከተኛል የሚል በሙሉ መገኘት ይችላል።

የጠረንጴዛ ዙርያ ውይይት 

ኣዘጋጅ  =     የኢትዮጵያውያውያን የጋር መድረክ በኖርዌይ
                     አራት ተወያዮች ተዘጋጅተዋል::
                     ውይይቱ ለሁሉም ከፍት ነው:: ለተወያዮች ጥያቄ
                     ማቅረብ ኣስተያየት መስጠት ይቻላል::
ቀን =           በመጪው ቅዳሜ ህዳር 10፣2009 ዓም
                     (ኖቬምበር 19፣2016)  

ቦታ=            ባትሬት 
አድራሻ       Fredsbogveien 24 A, Oslo, Norway

ሰዓት =         እኩለ ቀን (12 am) ይጀመራል። 


ፀጋዬ እሸቱ እውነት 



ጉዳያችን GUDAYACHN www.gudayachn.com

No comments:

ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።