Wednesday, November 2, 2016

ጥቅምት 23 የታሪካችን አካል (ቪድዮ)

ዛሬ ጥቅምት 23 ነው።እስካሁን አንድም ሐውልት ያልቆመላቸው ቀዳማዊ አፄ ኃይለ ስላሴ የነገሱት የዛሬ 86 ዓመት ጥቅምት 23/1923 ዓም በአሁኑ አራዳ (ፒያሳ) የሚገኘው ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ነበር።ሃውልት ብቻ አይደለም በስማቸው የተሰየመውን ከዩንቨርሲቲ እስከ የካቲት 12 ሆስፒታል ስም እየደለዝን የእራሳችንን ታሪክ ለመፃፍ የሞከርን ጉደኞች አሁንም እኛው ነን።
ይህም የታሪካችን አካል ነው።

ንግስት መነን የመጀመርያ የልጃገረዶች ትምህርት ቤት መስራች፣የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል እና በኢየሩሳሌም ያሉ ገዳማት ያደርጉት አስተዋፅኦ ሁሉ የሚጠቀስ ታሪክ ነበራቸው።ከሁሉም የኢትዮጵያ ሴቶችን ንግስት መነን እኩልነትን ለማጠናከር የለፉ ነበሩ።ስለ ዓለም የሴቶች እኩልነት እናወራለን እንጂ የእኛዎቹን ፈላስፋዎች ማድነቅ አልፈጠረብንም።አንድ ቀን ይህንን ሁሉ ምስቅልቅል የሚያስተካክል እና ወደ እራሳችን ሀብት የሚመለከት ትውልድ ይነሳል።እስከዛው ድረስ ግን ለማያውቀው  ጠብታ ተጠራቅሞ ጋን ይሞላል እና እንዲህ የጠብታ ያህል እንነግራለን።



ጉዳያችን GUDAYACHN www.gudayachn.com

No comments:

በአቴንስ፣ግሪክ የምትገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን ላለፉት 40 ዓመታት በላይ ስትጠቀምበት የነበረውን ፖሊጎኖ የሚገኘው ቤተክርስቲያን በፖሊስ ታሸገ።የቅዱስ ሲኖዶስ አፋጣኝ ምላሽ እየተጠበቀ ነው።

የአቴንስ ኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን የታሸገችበት የጉግል የእንግሊዝኛ ትርጉም እና የግሪክኛ ዋናው ኮፒ። በግሪክ አቴንስ የምትገኘው እና ወደ ግማሽ ክ/ዘመን አገልግሎት ስትሰጥ የነበረችው እና በአቴንስ ፖሊጎኖ የምትገኘው የ...