Tuesday, March 12, 2013

''በኢትዮዽያ ከ1999 ዓም(2007እኤአቆጣጠር) ወዲህ ብቻ አርባዘጠኝ ጋዜጠኞች ሃገር ትተው ሄደዋል'' አልጀዚራ (ቪድዮውን ይመልከቱ)

በኢትዮዽያ ሃሳብን የመግለጽ ነጻነት ብቻ ሳይሆን የማሰብ ነጻነት በእራሱ አስፈሪ ደረጃ ላይ መድረሳቸውን የሚያሳዩ በገፍ የሚሆኑ ማስረጃዎችን ማቅረብ ይቻላል።ለምሳሌ በታክሲ እየሄዱ የመብራት እና የውሃ መቋረጥን ብሶት ማውራት የሚፈራባት ነች-ሃገራችን።ይህንን ሰምተን በነጻ ጋዜጣ አለመኖር መማረር ''ቅንጦት'' ተብሎ ማሰብ ድፍረት ላይሆን ይችላል።ሃሳቡን መግለጽ የማይችል ትውልድ የ አዲስ ነገር ፈጠራ ባለቤት የመሆን እድሉ የሰማይ እና የመሬት ያህል ሩቅ ነው።አልጀዚራ የ ኢትዮዽያን የጋዜጠኞች እስር ቤት ማጎር እና የተቀሩት የሚሰደዱባት ሃገር የመሆንዋን እውነታ ዛሬ መጋቢት 3/2005ዓም ( march 13/2013 እኤአቆጣጠር) እንዲህ አቅርቦታል።በ ሪፖርቱ ላይ ከ1997 ዓም ወዲህ ብቻ አርባዘጠኝ ጋዜጠኞች ሃገር ትተው መሄዳቸውን  ያትታል።


Aljazeera: The Price of War on Terror in Ethiopia - March 12, 2013

1 comment:

Karl said...

This is really shame to EPRDF. If journalists can not speak out who will be a witness for a nation?
KARL.

በአቴንስ፣ግሪክ የምትገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን ላለፉት 40 ዓመታት በላይ ስትጠቀምበት የነበረውን ፖሊጎኖ የሚገኘው ቤተክርስቲያን በፖሊስ ታሸገ።የቅዱስ ሲኖዶስ አፋጣኝ ምላሽ እየተጠበቀ ነው።

የአቴንስ ኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን የታሸገችበት የጉግል የእንግሊዝኛ ትርጉም እና የግሪክኛ ዋናው ኮፒ። በግሪክ አቴንስ የምትገኘው እና ወደ ግማሽ ክ/ዘመን አገልግሎት ስትሰጥ የነበረችው እና በአቴንስ ፖሊጎኖ የምትገኘው የ...