ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Tuesday, May 6, 2014

''ኢትዮ ፈርስት'' የለቀቀውን ቪድዮ አየሁት።ፊልሙን የተረዳሁት በአራት ደረጃ ነው- በሚያሳዝን፣በሚያስደስት፣ በማይመስል እና የችግሩን ምንጭ ያድበሰበሰ በሚል


1/ የሚያሳዝን 

የተቃጠሉ ሆቴሎች እና ህንፃዎች የአምቦ ፍርድ ቤትን ጨምሮ መቃጠላቸውን ፊልሙ ያሳያል። እዚህ ላይ ያሳዝናል።

2/ የሚያስደስት  

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋኅዶ ቤተ ክርስቲያን በሺህ የሚቆጠሩ ከእስልምናም ሆነ ከሌላ እምነት የመጡትን ሁሉ ጨምራ ምንጣፍ አውጥታ በቅፅረ ግቢዋ እያሳደረች ማፅናናቷ፣ ወጥ እና እንጀራ የአምቦ ሕዝብ እያመጣ ከሐሙስ ዕለት ጀምሮ መመገቧ እና አሁንም ከሺህ በላይ ለሆኑ ተማሪዎች መጠለያ መሆኗን ተማሪዎች ሲመሰክሩ ፊልሙ ያሳያል። እዚህ ላይም በጣም ደስ የሚል ሥራ ተሰራ ያሰኛል።ቤተ ክርስቲያን እናትነንቷን አሳየች።

3/ የማይመስል  

ስለ ጠፋው ሕይወት አንዳች ነገር አልተነፈሰም የሞተውን ቁጥር መንገር አይደለም እንድያውም ''ከተማሪ የሞተ የለም'' የሚል ንግግር ከተማሪዎች ሲነገር ፊልሙ ያሳያል።ከነዋሪም ስንት ሰው እንደሞተም ፊልሙ አይተነፍስም።ይህ ብቻ አይደለም ግጭቱ የተነሳበትን ምክንያት ከአዲስ አበባ ማስተር ፕላን በዘለለ ፊልሙ ሊያጎላው የፈለገው ''አራምባና ቆቦ'' የሆነ ጉዳይ ነው አንዴ 'ባህር ዳር በነበረው የስፖርት ውድድር በነበረው ግጭት የተናደዱ'፣ይላል መልሶ አፄ ምኒልክን ያነሳል ቀጥሎ ቴዲን ያነሳል። ይህ የተጨመረ ቅመም ነው።ህዝብን ለማጋጨትም የገዢዎቻችን ዝብዘባ ነች። እንበል አንድ ሁለት የዞረባቸው እና ''የሜጫ'' አስተሳሰብ የያዙ ደካማ ተማሪዎች አሉ እንበል የእነርሱን ሃሳብ ሚድያ ላይ መናገር እና ማጉላት  ምን ሊያስከትል እንደሚችል ገዢዎቻችን ያውቃሉ።ግን አሁንም የሚነግሩን የፅንፈኞችን እንጉርጉሮ ነው።ጉዳዩን በባህር ዳር እና በምኒሊክ ዙርያ ማዞር ምን ማለት እንደሆነ ግልፅ ነው።እናም ፊልሙ በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ ለመምታት ያሰበ ይመስላል።ማጋጨት ተክናቹበታል።

4/ ፊልሙ የችግሩን ምንጭ አልጠቀሰም 

ኢህአዲግ ሁሌ የሚረሳው ነገር በብሄር እና  በቋንቋ ምክንያት ለምትፈሰው እያንዳንዷ ጠብታ ደም ኢህአዲግ/ወያኔ ተጠያቂ መሆኑን ነው።ኢትዮጵያ በታሪክ በእንደዚህ ደረጃ በአንድነቷ እና በህልውናዋ ላይ የተቃጣ መንግስታዊ የዘር ፖለቲካ መርዝ ተረጭቶባት አያውቅም።አዲስ አበባ ከኦሮምኛ ጋር ጥያቄውን ያወሳሰበው እራሱ ወያኔ ነው።ኢህአዲግ/ወያኔ በ 1997 ዓም አዲስ አበባን አንዴ ፊንፊኔ ብያለሁ የኦሮምያ ዋና መቀመጫ ሆነች ሲለን መልሶ ደግሞ ወደ አዳማ ቀይሬዋለሁ ሲለን፣ ሌላ ጊዜ አቦይ (የተቀበረውን መርዝ ያውቃሉ እና) እኛ ከሌለን ኢትዮጵያ በማግስቱ ትከፋፈላለች ሲሉን እንዳልንበር ለአምቦ ብጥብጥ ተጠያቂዎቹ ፅንፈኛ ኃይሎች ብቻ ሳይሆኑ እራሱ ኢህአዲግ/ወያኔ ያፀደቀው የጎሳ ፖለቲካ ፌድራሊዝም ነው።

ይህ እንደሚሆን ደግሞ ሕዝብ የተናገረው ከዛሬ 23 ዓመት በፊት ነበር።''ይህ አይሆንም አንድነታችን እንደ ብረት የጠነከረ እየሆነ ነው'' እያለ ስዋሸን የነበረው ደግሞ ኢህአዲግ/ወያኔ ነው። በመሆኑም የችግሩ ምንጭ ዋናው ጎሳን መሰረት ያደረገ ኢትዮጵያን ለመበታተን የቆመው የኢህአዲግ/ወያኔ ከፋፋይ ፌድራሊዝም ነው። እናም ተጠያቂውም ሆነ የችግሩ ምንጭ እና ፅንፈኞች ኢትዮጵያ ላይ እንዲዘባበቱባት የሕግ ድጋፍ የሰጣቸው አሁንም ኢህአዲግ/ወያኔ ነው። አሁንም የችግሩ ምንጭ እራሱ ኢህአዲግ/ወያኔ እስካለ ድረስ ተመሳሳይ ችግሮች ገና ብዙ ልናይ እንችላለን።እንደ ኢህአዲግ እቅድ የአሩሲው የተቆረጠ እጅ ሃውልት በ ሃያ ሚልዮን ብር ሲገነባ እና ኢቲቪ ባለፈው ወር እንደ ዜና ሲናገር ነገሩን ጨርሶታል።አሁንም ለእያንዳንዷ የደም ጠብታ ዋና ምንጩ የኢህአዲግ የጎሳ ፖለቲካ ነው።ሌላው አጫፋሪ ነው።''ኢትዮ ፈርስት'' የሸሸገን ወይንም ለመናገር የፈራው እውነታም ይህንኑ የችግሩን ዋና ምንጭ ነው።

ጉዳያችን
ሚያዝያ 28/2006 ዓም 

No comments:

ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።