ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Tuesday, October 31, 2017

ለኦስሎ፣ኖርዌይ የቤተ ክርስቲያን ጨረታ በተጨመሩት ጥቂት ቀናት ምዕመናን ተጠቅመው የቤተ ክርስቲያንን አቅም ማጠናከር እንዲቀጥሉ ተጠየቁ።

በኦስሎ፣ኖርዌይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስት ተዋህዶ ቅዱስ ገብርኤል ወአቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን የህንፃ ጨረታ ምዕመናን በተራዘሙት ጥቂት ቀናት በመጠቀም የቤተ ክርስቲያንን አቅም እንዲያጠናክሩ ተጠየቁ።ይህንን የጠየቀው የቤተክርስያኒቱ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ጋር በጥምረት የሚሰራው የህንፃ ኮሚቴ ነው። ጨረታው የተራዘመበትን ምክንያት ኮሚቴው ማምሻውን በቫይበር ግሩፕ ለሚከታተሉት ምዕመናን በኢሜል ያስታወቀ ሲሆን የጎፈንዱ አካውንትም (የጎፈንዱን አካውንት ለመክፈት ይህንን ይጫኑ)  እስከ ጨረታው መጀመርያ ቀን ድረስ እንደሚቆይ ለማወቅ ተችሏል። የህንፃ ኮሚቴው ማምሻውን የላከው ኢሜል ከእዚህ በታች የሚከተለው ነው።


ሰብሕዎ ለአምላክነ (መዝሙር) ያድምጡት 




ጉዳያችን GUDAYACHN

 www.gudayachn.com

No comments:

''አክቲቪዝም ከጆርናሊዝም'' የደባለቀባቸው ዩቱበሮች በአማራ ክልል የሚፈሰው የመከላከያ እና የአማራ ክልል ህዝብ ደም አልታያቸው ብሏል። በኢትዮጵያ ህዝብ አንድ ሊባሉ ይገባል።

የሰው ደም እየፈሰሰ መከላከያና የአማራ ክልል ታጣቂ ኃይል አይነጋገር የሚሉት በውጪ ሀገር ሶፋ ላይ የተቀመጡት መሆናቸውን ልብ ይሏል። የሰላም ንግግሮችን ለማጣጣል የሚሞክሩትን አጥብቀን መቃወም ኢትዮጵያዊ የውዴታ ግዴታችን ...