ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Thursday, November 12, 2015

ኢህአዴግ/ህወሃት የተከሰተውን ድርቅ ጆሮ ተነፍጎታል። የአሜሪካ ኤምባሲ አሜሪካ የላከችው እርዳታ ድሬዳዋ ላይ መራገፉን የሚያሳይ የአንድ ደቂቃ ፊልም ለቀቀ።

የኢትዮጵያ ቴሌቭዥንም ሆነ ራድዮ  15 ሚልዮን ሕዝብ አደጋ ላይ ስለመሆኑ ምንም ነገር አላወሩም።አዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ 97 ሚልዮን ዶላር የሚያወጣ የምግብ ዕርዳታ  አሜሪካ ሰጠች የሚል መግለጫ አውጥቷል።በአዲስ አበባ እና በሌሎች የኢትዮጵያ ክፍል የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ሊብያ ላይ በአይኤስ ኤስ የታረዱት ኢትዮጵያውያንን ዜና ሊያድበሰብስ የነበረ ኢህአዴግ/ህወሃት በድርቁ ጉዳይ ላይም ተመሳሳይ አካሄድ እያሳየ ስለሆነ በሊብያው ጉዳይ ላይ ሕዝብ ቀድሞ በመውጣት ኢህአዴግ/ህወሃት ለጉዳዩ ትኩረት እንዲሰጥ እንዳስገደደ ሁሉ አሁንም ሕዝብ ማስገደድ አለበት የሚሉ በርካታ አስተያየቶች እየተሰሙ ነው።

''ዩኤስ ኤይድ'' ከፊልሙ በታች በለጠፈው ዩቱዩብ ላይ  ''በኢትዮጵያ እራሳቸውን እና ቤተሰባቸውን ለመመገብ በቂ ምግብ ለሌላቸው ...'' የሚሉ ቃላትን ይዟል።

ከእዚህ በታች የሚታየው የአንድ ቂቃ ፊልም አዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ አሜሪካ 97 ሚልዮን ዶላር የሚያወጣ ምግብ ለኢትዮጵያ መስጠቷን የሚያሳየውን መግለጫ በለጠፈበት ማኅበራዊ ድረ-ገፅ ላይ የተለጠፈ ነው።



Film Source:- USAID Youtube


ጉዳያችን GUDAYACHN BLOG

No comments:

ህወሓት ሰሜን ወሎ ራያን ወርሮ የገጠር ወረዳዎችን እየዘረፈ ነው። ህዝብ ሲዘረፍ እና በአስር ሺዎች ሲፈናቀሉ የመንግስት የፖለቲካም ሆነ የወታደራዊው አመራሮች ዝምታቸው ከተጠያቂነት አያድናቸውም።

በሰሞኑ የህወሓት ወረራ ቆቦ ተፈናቅለው የገቡ የሰሜን ወሎ ተፈናቃዮች  በከፊል ፎቶ፡ ቢቢሲ ሚያዝያ 20፣2024 እኤአ ''ቅጥ አምባሩ የጠፋው'' የፕሪቶርያው ውል   ''ስኩዌር ዋን&#...