Wednesday, April 30, 2014

ለሀገራቸው የተሰዉ በርካታ ጀግና ኢትዮጵያውያንን ያፈራችው አምቦ እያነባች ነው።

ለቪኦኤ የአማርኛው አገልግሎት የአይን እማኞችን እንደገለፁት

- ቁጥሩ ያልታወቀ ሰው ተገድሏል፣

- አንድ ባንክ ተቃጥሏል፣

- ሶስት ህንፃዎች ተቃጥለዋል፣

- ብዙ ቤተሰብ ተበታትኖ ከቤት ወጥቶ ይገኛል።

ኢሳት የአይን እማኞችን ጠቅሶ እንደዘገበው ደግሞ በተማሪዎቹ ላይ እና ህዝቡ ላይ ሲተኩሱ የነበሩት የመንግስት ወታደሮች አልመው የሚተኩሱ ''ስናይፐሮች'' ነበሩ ብሏል።

እጅግ አሳዛኝ ተግባር።ኢህአዲግ በትክክል ሀገር ማስተዳደር አለመቻሉን መግለፅ ያለበት ጊዜ ላይ ነው።ሕይወታቸው ላለፉት ሁሉ እረፍተ ነፍስን ይስጥልን ለቤተሰብ መፅናናንትን። ለሀገራቸው የተሰዉ ጀግና ኢትዮጵያውያንን ያፈራችው አምቦ እያነባች ነው። በኢህአዲግ የሚታዘዙት የመገናኛ ብዙሃን ዝምታ አሳፋሪ ነው።ኢትዮጵያ ልጆቿ በሰበብ አስባቡ እየረገፉባት ነው።



ጉዳያችን GUDAYACHN BLOG

No comments:

7ኛው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ግንቦት 24፣2018 ዓም በከፍተኛ የሕዝብ ተሳትፎ ተጠናቋል።

ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ በሰባተኛው ብሔራዊ ምርጫ ድምፅ ሲሰጡ። ስለምርጫው ዝርዝር ጉዳይ ምን ያውቃሉ? ✓ ሰባተኛው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ 42 ፓርቲዎች እና 73 የግል ተወዳዳሪዎች ለተለያዩ ምክር ቤቶች ዕጩዎች ...