Monday, June 24, 2013

''አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ሰው አልገደለም።'' አቶ ኦባንግ ሜቶ (ቪድዮ)

በእስራኤል የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን አቶ ኦባንግ ሜቶ ''የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ'' (http://www.solidaritymovement.org) ሊቀመንበርን ንግግር እንዲያደርጉ ጋብዘው ነበር።''ኢትዮጵያን እናድን አንድነት ማህበር በእስራኤል'' በሚል ማኅበር ስር የተሰባሰቡት ወጣት ኢትዮጵያውያንን በከበረ ሰላምታ በማቅረብ ንግግራቸውን የጀመሩት ኦባንግ ''አቶ መለስ የሚነዳው ባቡር የጥላቻ ባቡር ነው.....አሁን ባቡሩ እየቆመ ነው'' ብለዋል።አቶ ኦባንግ ባለፈው ሳምንት የአሜሪካ ምክርቤት የውጭ ፖሊስ ንዑስ ኮሚቴ ቀርበው በተናገሩት ንግግር የብዙ ኢትዮጵያውያንን ልብ አኩርተዋል። አቶ ኦባንግ በአሜሪካ ምክርቤት ቀርበው ''እኛ አሜሪካኖችንን ነፃነት እንዲሰጡን አንለምንም ይህንን እኛ ማድረግ እንችላለን'' ነበር ያሉት።


አቶ ኦባንግ በእስራኤል ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ያደረጉት ንግግር ቪድዮ ይመልከቱ።



ጉዳያችን GUDAYACHNgetachewb221@gmail.com

No comments:

በአቴንስ፣ግሪክ የምትገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን ላለፉት 40 ዓመታት በላይ ስትጠቀምበት የነበረውን ፖሊጎኖ የሚገኘው ቤተክርስቲያን በፖሊስ ታሸገ።የቅዱስ ሲኖዶስ አፋጣኝ ምላሽ እየተጠበቀ ነው።

የአቴንስ ኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን የታሸገችበት የጉግል የእንግሊዝኛ ትርጉም እና የግሪክኛ ዋናው ኮፒ። በግሪክ አቴንስ የምትገኘው እና ወደ ግማሽ ክ/ዘመን አገልግሎት ስትሰጥ የነበረችው እና በአቴንስ ፖሊጎኖ የምትገኘው የ...