Wednesday, December 23, 2015

ሶማልያ ውስጥ ማንም ሰው የክርስቶስን ልደት በዓል እንዳያከበር ጥብቅ መንግስታዊ መግለጫ ተሰጠ።Somali government bans Christmas celebrations


ማልያ 

የሶማልያ መንግስት የሃይማኖት ጉዳይ ዳይሬክተር፣ሼክ መሐመድ ኬይሮው ማንም ሰው በሶማልያ ውስጥ የክርስቶስን ልደት እንዳያከብር ጥብቅ ትዕዛዝ አስተላለፉ።ባለሥልጣኑ ''የልደት በዓል የሚያከብሩትን በሙሉ አስጠነቅቃለሁ።የክርስቲያኖች በዓል የሆነው የልደት በዓል  ለእስላማዊቷ አገር ምንም ማለት አይደለም'' ብለዋል። እንደ ሮይተርስ ዘገባ ባለሥልጣኑ በሞቃዲሾ በየትኛውም ስፍራ እና በሶማልያ ውስጥ የክርስቶስን ልደት የሚያከብሩ ካሉ ቅጣት እንደሚጠብቃቸው የሚገልፅ ማሳሰብያ እና ትዕዛዝ ለሶማሌ ፖሊስ እና የደህንነት ቢሮ መተላለፉን ገልፀዋል።

ባለሥልጣኑ ይህንን ይበሉ እንጂ በሶማሌ በሺ የሚቆጠሩ የተባበሩት መንግሥታት ሰላም አስከባሪ ሰራዊት ይገኝባታል።ይህ ሰራዊት ደግሞ ከቡሩንዲ፣ዑጋንዳ እና ኬንያ  የተውጣጣ ሲሆን ባብዛኛው ክርስቲያኖች መሆናቸውን የሮይተርስ ዜና ያትታል።ኢትዮጵያም ሰራዊቷ በሱማልያ እንደሚገኝ መነገሩ ይታወሳል።

የሮይተርን ሙሉ ዜና ለማንበብ ከእዚህ በታች ያለውን ማያያዣ ይጫኑ።

ምንጭ: ሮይተርስ  Reuters   

ጉዳያችን GUDAYACHN
www.gudayachn.com 
ታህሳስ 13/2008 ዓም (December 23/2015)

No comments:

በአቴንስ፣ግሪክ የምትገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን ላለፉት 40 ዓመታት በላይ ስትጠቀምበት የነበረውን ፖሊጎኖ የሚገኘው ቤተክርስቲያን በፖሊስ ታሸገ።የቅዱስ ሲኖዶስ አፋጣኝ ምላሽ እየተጠበቀ ነው።

የአቴንስ ኪዳነምሕረት ቤተክርስቲያን የታሸገችበት የጉግል የእንግሊዝኛ ትርጉም እና የግሪክኛ ዋናው ኮፒ። በግሪክ አቴንስ የምትገኘው እና ወደ ግማሽ ክ/ዘመን አገልግሎት ስትሰጥ የነበረችው እና በአቴንስ ፖሊጎኖ የምትገኘው የ...