Wednesday, December 23, 2015

ሶማልያ ውስጥ ማንም ሰው የክርስቶስን ልደት በዓል እንዳያከበር ጥብቅ መንግስታዊ መግለጫ ተሰጠ።Somali government bans Christmas celebrations


ማልያ 

የሶማልያ መንግስት የሃይማኖት ጉዳይ ዳይሬክተር፣ሼክ መሐመድ ኬይሮው ማንም ሰው በሶማልያ ውስጥ የክርስቶስን ልደት እንዳያከብር ጥብቅ ትዕዛዝ አስተላለፉ።ባለሥልጣኑ ''የልደት በዓል የሚያከብሩትን በሙሉ አስጠነቅቃለሁ።የክርስቲያኖች በዓል የሆነው የልደት በዓል  ለእስላማዊቷ አገር ምንም ማለት አይደለም'' ብለዋል። እንደ ሮይተርስ ዘገባ ባለሥልጣኑ በሞቃዲሾ በየትኛውም ስፍራ እና በሶማልያ ውስጥ የክርስቶስን ልደት የሚያከብሩ ካሉ ቅጣት እንደሚጠብቃቸው የሚገልፅ ማሳሰብያ እና ትዕዛዝ ለሶማሌ ፖሊስ እና የደህንነት ቢሮ መተላለፉን ገልፀዋል።

ባለሥልጣኑ ይህንን ይበሉ እንጂ በሶማሌ በሺ የሚቆጠሩ የተባበሩት መንግሥታት ሰላም አስከባሪ ሰራዊት ይገኝባታል።ይህ ሰራዊት ደግሞ ከቡሩንዲ፣ዑጋንዳ እና ኬንያ  የተውጣጣ ሲሆን ባብዛኛው ክርስቲያኖች መሆናቸውን የሮይተርስ ዜና ያትታል።ኢትዮጵያም ሰራዊቷ በሱማልያ እንደሚገኝ መነገሩ ይታወሳል።

የሮይተርን ሙሉ ዜና ለማንበብ ከእዚህ በታች ያለውን ማያያዣ ይጫኑ።

ምንጭ: ሮይተርስ  Reuters   

ጉዳያችን GUDAYACHN
www.gudayachn.com 
ታህሳስ 13/2008 ዓም (December 23/2015)

No comments:

7ኛው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ግንቦት 24፣2018 ዓም በከፍተኛ የሕዝብ ተሳትፎ ተጠናቋል።

ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ በሰባተኛው ብሔራዊ ምርጫ ድምፅ ሲሰጡ። ስለምርጫው ዝርዝር ጉዳይ ምን ያውቃሉ? ✓ ሰባተኛው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ 42 ፓርቲዎች እና 73 የግል ተወዳዳሪዎች ለተለያዩ ምክር ቤቶች ዕጩዎች ...