ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Saturday, December 19, 2015

የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ ያዘጋጀው ሰልፍ ታህሳስ 8/2008 ዓም (ደሴምበር 18/2015 ዓም) በኖርዌይ ፓርላማ ፊት ለፊት ተደረገ።

የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ ያዘጋጀው ሰልፍ ባለፈው ታህሳስ 8/2008 ዓም (ደሴምበር 18/2015 ዓም) በኖርዌይ ፓርላማ ፊት ለፊት ተደርጎ ነበር።የሰልፉ አላማ በኦሮምኛ ተናጋሪ ኢትዮጵያውያን ላይ የተፈፀመውን ግድያ፣በጎንደር ሕይወታቸው በወያኔ ወታደሮች የተገደሉትን በመቃወም እና ለሱዳን ሊሰጥ በዝግጅት ላይ ነው የተባለው የድንበር ውል በመቃወም ነበር።

ሰልፉ ከመሃል ኦስሎ ተነስቶ ወደ ኖርዌይ ፓርላማ በማምራት ለኖርዌይ ፓርላማ በኢትዮጵያ እየተፈፀመ ያለውን ግፍ እና የሰልፉን አላማ የያዘ ደብዳቤ በመስጠት ተፈፅሟል። የፓርላማው ተወካይም ሰልፈኞቹ ወዳሉበት በመምጣት ወረቀቱን ከተቀበለ በኃላ ለሚመለከተው ክፍል እንደሚያደርስ ለተሰብሳቢዎቹ ቃል ገብቷል።

ከእዚህ በተጨማሪ  በሰላማዊ ሰልፉ ላይ ከዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌይ አመራር አቶ ዳንኤል አበበ፣ከአርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነት እና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ዶ/ር ሙሉዓለም አዳም፣ ከኖርዌይ ሸንጎ አቶ ግደይ ዘርአፅዮን፣ከኢትዮጵያ ማኅበረሰብ በኖርዌይ ወ/ሮ ዙፋን አማረ ተገኝተው በአገራችን በስርዓቱ እየደረሰ ያለውን ግፍ በማብራራት ንግግር አድርገዋል።

የሰልፉን ፎቶዎች በከፊል ከእዚህ በታች ይመልከቱ (ፎቶ ጉዳያችን)










ሰልፈኛው ወደ ኖርዌይ ፓርላማ ሲያመራ 
 የኖርዌይ ፓርላማ ተወካይ 






ጉዳያችን GUDAYACHN BLOG

No comments:

ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።