Pages

Pages

Thursday, January 8, 2015

የዘንድሮው የ2007 ዓም የከተራ እና ጥምቀት በዓል በአራቱም የኖርዌይ ከተሞች የሚገኙት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አብያተ ክርስቲያናት ታቦታት በሕብረት እና በአንድቤተ ክርስቲያን ይባርካሉ።

የዘንድሮው የጥምቀት በዓል በኦስሎ፣ኖርዌይ የሚከበርበት የማየሽትዋ ቤተ ክርስቲያን 

የዘንድሮው የ2007 ዓም የከተራ እና ጥምቀት  በዓል በአራቱም የኖርዌይ ከተሞች ማለትም በስታቫንገር፣ክርስቲያን ሳንድ፣ትሮንዳይም እና በርገን የሚገኙት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አብያተ ክርስቲያናት ታቦታት በሕብረት እና በአንድቤተ ክርስቲያን ማለትም በኖርዌይ ዋና ከተማ በኦስሎ፣ማየሽትዋ ሺርከን 84 (Majorstuen kirks, Kirkeveien 84)፣ያከብራሉ።በበዓሉ ላይ ከመላዋ ኖርዌይ እና ከኖርዌይ ውጭ የሚመጡ ምዕመናን ይታደማሉ።አቡነ ኤልያስ ህዝበ ክርስቲያኑን ይባርካሉ።

ቦታ - ማየሽትዋ ሺርከ፣ሺርከ ቫየን 84 (Majorstuen kirks, Kirkeveien 84)
ቀን - ጥር 16 እና 17/2007 ዓም (ጃንዋሪ 24 እና 25/2015)
ሰዓት - ጥር 16/2007 ዓም (ጃንዋሪ 24/2015) ከቀትር በኃላ 8 ሰዓት (2Pm) ማለትም  (14 ሰዓት ) ላይ ይጀመራል።





No comments:

Post a Comment

አስተያየትዎን እዚህ ላይ ይስጡ