ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Sunday, March 9, 2014

ነፃነት እንፈልጋለን! የዛሬ የኢትዮጵያ ሴቶች ድምፅ በአዲስ አበባ አውራ ጎዳናዎች (ቪድዮ)

ከ እዚህ በታች የተፃፈው ፅሁፍ የተገኘው ከሰማያዊ ፓርቲ ፌስ ቡክ ገፅ ላይ ነው።እንዲህ ይነበባል -

''ለነጻነት የሮጡት ታሰሩ ዛሬ በተካሄደው የሴቶች 5ሺሜትር ሩጫ ላይ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ‹‹ለነጻነት እንሩጥ›› በሚል መሪ ቃል የተለያዩ ፖለቲካዊ ጥያቄዎችን በማንሳት ተሳታፊውን ሲያነቃቁ ውለዋል፡፡ በሩጫው ላይ ከተነሱ ጥያቄዎችና መፈክሮች መካከል ርዕዮትና ሌሎች የህሌና እስረኞች ይፈቱ፣ መብትን መጠየቅ አሸባሪነት ከሆነ አሸባሪዎች ነን፣ ውሃ ናፈቀን፣ መብራት ናፈቀን፣ ነጻነት፣ እኩልነት፣ ፍትህ፣ ዴሞክራሲ፣ ውሸት ሰለቸንና የመሳሰሉት ይገኙበታል፡፡ ከመነሻው የጀመረው የተቃውሞ ድምጽ እስከ ማብቂያው የቀጠለ ሲሆን ሲከታተሏቸው የዋት ፖሊስና የደህንነት ኃይሎች ሩጫውን ጨርሰው ሲገቡ አስረዋቸዋል፡፡ በአሁኑ ሰዓት የሩጫው ተሳታፊዎች ታስረው ይገኛሉ፡፡''


ጉዳያችን GUDAYACHN BLOG

No comments:

ወቅታዊ የዓለም ሁኔታ እንድንነታረክ ዕድል የሚሰጥ አይደለም።ብንነቃ መልካም ነው።

========== ጉዳያችን ወቅታዊ ========== የዓለም ታሪክ እንደሚያስተምረን ዓለም በወሳኝ የእጥፋት(turning point) ታሪኮች ውስጥ አልፋለች። እነኝህ የእጥፋት ጊዜዎች የዋዛና የፈዛዛ ጊዜ አይደሉም።መላው ዓለ...