ፕሮፌሰር ሰገነት ቀለሙ
ፕሮፌሰር ሰገነት ቀለሙ በዓለም ላይ ካሉት አምስቱ ምርጥ ሴት ሳይንቲስቶች ውስጥ አንዷ እና በአፍሪካ እና ከአረብ ሃገራት ብቸኛ ሆነው የተመረጡ መሆናቸውን የዩኔስኮ ድረ-ገፅ ገልጧል።
ድረ-ገፁ አክሎም የምርጫውን ሂደት ሲያስረዳ አንድ ሺህ ዓለም አቀፍ ሳይንቲስቶች ኔትዎርክ አማካይነት ምርጫውን እንደሚያደርግ፣ በመጨረሻ አስራ ሁለት አባላት ባሉት ዓለም አቀፍ ሳይንሳዊ ማኅበረሰብ (International Scinitfic Community) አማካይነት ውሳኔ እንደሚያገኝ ያብራራል።
ፕሮፌሰር ሰገነት ቀለሙ መቀመጫውን ናይሮቢ ኬንያ ያደረገው በአካባቢ ስነ-ምህዳር ላይ የሚሰራው International Center for Insect Physiology and Ecology (ICIPE) ዳይሬክተር ጀነራል ሆነው ይሰራሉ።
ዩኔስኮ ሽልማቱን አስመልክቶ የሰጠውን ዜና ከእዚህ በታች ባለው ሊንክ ይመልከቱ።
http://www.unesco.org/new/fileadmin/MULTIMEDIA/HQ/SC/pdf/PressR_L-OREAL_UNESCO_2014_EN.pdf
ጉዳያችን
መጋቢት 12/2006 ዓም