ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Friday, March 21, 2014

ኢትዮጵያዊቷ ፕሮፌሰር ሰገነት ቀለሙ በዓለም ዙርያ ካሉ 1000 ሳይንቲስቶች ውስጥ ከተመረጡት ከዓለም አምስቱ ምርጥ ሳይንቲስቶች ከአፍሪካ እና አረብ ሃገራት ደግሞ ብቸኛ ሆነው የ 2014 ዓም የዩኔስኮ 'ሎሬአል' ሽልማት አሸናፊ ሆኑ።

ፕሮፌሰር ሰገነት ቀለሙ

ፕሮፌሰር ሰገነት ቀለሙ በዓለም ላይ ካሉት አምስቱ ምርጥ ሴት ሳይንቲስቶች ውስጥ አንዷ እና በአፍሪካ እና ከአረብ ሃገራት ብቸኛ ሆነው የተመረጡ መሆናቸውን የዩኔስኮ ድረ-ገፅ ገልጧል።

ድረ-ገፁ አክሎም  የምርጫውን ሂደት ሲያስረዳ አንድ ሺህ ዓለም አቀፍ ሳይንቲስቶች ኔትዎርክ አማካይነት ምርጫውን እንደሚያደርግ፣ በመጨረሻ አስራ ሁለት አባላት ባሉት ዓለም አቀፍ ሳይንሳዊ ማኅበረሰብ (International Scinitfic Community) አማካይነት ውሳኔ እንደሚያገኝ ያብራራል።

ፕሮፌሰር ሰገነት ቀለሙ መቀመጫውን ናይሮቢ ኬንያ ያደረገው በአካባቢ ስነ-ምህዳር ላይ የሚሰራው  International Center for Insect Physiology and Ecology (ICIPE) ዳይሬክተር ጀነራል ሆነው ይሰራሉ።

ዩኔስኮ ሽልማቱን አስመልክቶ የሰጠውን ዜና ከእዚህ በታች ባለው ሊንክ ይመልከቱ።
http://www.unesco.org/new/fileadmin/MULTIMEDIA/HQ/SC/pdf/PressR_L-OREAL_UNESCO_2014_EN.pdf

ጉዳያችን
መጋቢት 12/2006 ዓም 

የመጀመርያዋ የኢትዮጵያ ሴት ፕሬዝዳንት የነበሩት ክብርት አምባሳደር ሣህለወርቅ ዘውዴን በክብር አለመሸኘት የኢትዮጵያን ክብር ብቻ ሳይሆን ለሴት ልጅ ያለንን የክብር ልኬት የሚያሳይ ነው።

የቀድሞ የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ሣህለወቅ ዘውዴ ጉዳዩ የዲሞክራሲ ባሕላችን ያኋልዮሽ ጉዞ ቁልጭ አድርጎ ያሳያል። የኢትዮጵያ ታዳጊ ሴትና ወንድ ልጆች የምናስተምራቸው ምንድን ነው? የመጀመርያዋ ሴት ፕሬዝዳንት ሲሰናበቱ እንዴት...