Monday, February 17, 2014

'' ለኢትዮጵያ መንግስት ተላልፈን የማንሰጥ ለመሆናችን ዋስትና እና ጥገኝነት እንዲሰጠን እንፈልጋለን'' የኢትዮጵያ አየር መንገድ ጠለፋ ጉዳይ (latest)

 የኢትዮጵያ አየር መንገድ ንብረት የሆነው የተጠለፈው አይሮፕላን 

-ከ አዲስ አበባ ወደ ሮም ይበር የነበረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራ ቁጥር 702 ጄኔቭ ላይ ዛሬ የካቲት 10/2006 ዓም በማዕከላዊ የአውሮፓ ሰዓት ከማለዳው 12 ከ 02 ሲሆን  እንዲያርፍ ተገዷል።

-  ሁሉም ተሳፋሪዎች እና አይሮፕላኑም በደህና ሁኔታ ላይ ይገኛሉ።

- ለ 2 ሰዓት ከ 45 ደቂቃ ተዘግቶ የነበረው የጀኔቭ አየር ማረፍያ  ተመልሶ ተከፍቷል።

- ጠላፊው ረዳት አብራሪው ነው።

- ዋና አብራሪው ወደ ሽንት ቤት ሲሄድ ረዳቱ ሽንትቤቱን ቆለፈበት እና አይሮፕላኑን ጠለፈው።

- አብራሪው ካለ አንዳች ማንገራገር እጁን ለስዊዝ ፖሊስ ሰጥቷል።ጥገኝነት እንዲሰጠውም ይፈልጋል።

- አይሮፕላኑ ውስጥ ከነበሩት ተሳፋሪዎች 143ቱ ጣልያናውያን ናቸው።

- ''ዘ ሎካል'' የተሰኘው የስዊዝ ጋዜጣ ዛሬ እንደዘገበው በስዊዘርላንድ ሕግ መሰረት ወንጀሉ እሰከ 20 አመት እስር ሊዳርግ ይችላል።

- ''ዘ ሎካል''  ጋዜጣ  አክሎም በድረ-ገፁ ላይ የጠላፊውን ቃል በድምፅ እንዲህ ሲል አሰምቷል '' ለኢትዮጵያ መንግስት ተላልፈን የማንሰጥ ለመሆናችን ዋስትና እና ጥገኝነት እንዲሰጠን  እንፈልጋለን''
''The local'' Switzerland news paper http://www.thelocal.ch/20140217/ethiopian-plane-lands-in-geneva-after-hijacking

ጉዳያችን
የካቲት 10/2006 ዓም 

No comments:

''ሙዝ አትብላ! ጦጣዎች ከጫካ ሊመጡ ይችላሉ።'' ዓይነቱ የጀዋር ጊዜው ያለፈበት ትንተና በኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ላይ።

ቀይ ባሕር ዛሬ በዩቱብ አገኘን ብላችሁ በኢትዮጵያ የባሕር በር ጉዳይ ላይ የምትሳለቁ የዘመናችን ባንዳዎች ግዴላችሁም ጊዜ እና ትውልድ ይፈርዳል! እናንተን ብቻ ሳይሆን ልጆቻችሁም ''አባታቸው በዩቱብ ኢትዮጵያ ...