ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Friday, February 7, 2014

ወደ አዋጅነት ይቀየራል የተባለው ‹የሃይማኖት ተቋማት ምዝገባና የዕድሳት አገልግሎት›› ረቂቅ መመርያ ኃላፊነት የጎደለው እንዳይሆን የብዙዎች ስጋት ነው።

ፎቶ- ሐዋሳ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን 

 የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ከ‹‹ኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ›› ጽ/ቤት ጋራ በመተባበር ያዘጋጀውና ከጥር 30 – የካቲት 2 ቀን 2006 ዓ.ም. በሐዋሳ – ሌዊ ሪዞርት ‹የሃይማኖት ተቋማት ምዝገባና የዕድሳት አገልግሎት›› ረቂቅ ላይ ለውይይት እንደሚቀርብ ለማወቅ ተችሏል። ይህ ከመመሪያ ወደ ዐዋጅነት ይቀየራል እየተባለ የሚነገርለት መመርያ ምንነት እስካሁን በዝርዝር አልታወቀም።

‹ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የአዋጁ ረቂቅ እንዲሰጣት እና አስተያየትና አቋም ለመውሰድ ለፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ያቀረበችው ጥያቄ ምላሽ  አለማግኘቱን ሐራ ተዋሕዶ የተሰኘው ብሎግ ጥር 28/2006 ዓም ገልጧል።

በኢትዮጵያ ከ 1952 ዓም ወዲህ ምንም አይነት ሃይማኖትን የተመለከተ አዋጅ  ወጥቶ አያውቅም። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ከ 40 ሚልዮን በላይ ተከታዮች ያሏት እና ክርስትና ከተመሰረተ ጀምሮ ላለፉት ከ 2000 አመታት በላይ ለሆኑ ዘመናት  በኢትዮጵያ መንፈሳዊ አገልግሎት ለመስጠት የፍቃድ እና የምዝገባ መስፈርት ተጠይቃ እንደማታውቅ ይታወቃል።ደርግም በዘመኑ ምንም አይነት ሃይማኖታዊ አዋጅ አለማውጣቱ ይታወሳል።ይህ ወደ አዋጅ ያድጋል የተባለው መመርያ ኃላፊነት የጎደለው እንዳይሆን የብዙዎች ስጋት ነው።

ጉዳያችን
ጥር 30/2006 ዓም 

No comments:

ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።