ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Thursday, February 6, 2014

እባክህ ክፈለኝ ያስተማርኩበትን (አጭር ግጥም የኢትዮጵያን ገበሬ ለተሳደቡት የኢህአዲግ ከፍተኛ ባለስልጣን)



አንጀቴን አስሬ ፣
ከእኔ ይቅር ብዬ አንተን አስተምሬ፣

ዛሬ ያወቀ መስሎት…. ''ባዶ እግር'' ነህ አለኝ፣
  ትስቅብኝ ጀመር ጫማ ስለሌለኝ፣

ባለጫማ መሆን  መቼ ጠፋኝ እኔ፣
መልበስ መሽቀርቀሩ አንተን አደንቁሬ።

ላስተምርህ ብዬ እንጂ ነገ እንድትሻገር፣
መስሎኝ----እኔ መራቆቴ ላንተ ልሆን ማገር።

ግና ምን ያደርጋል አንተም አልተማርክም፣
    ማስተዋል ነስቶሃል ከእኔ አልተሻልክም።

እናም ---እኔ ባዶ ሆኘ ያለበስኩበትን፣
            እባክህ  ክፈለኝ ያስተማርኩበትን።

ጉዳያችን
ጥር 30/2006
ምሽት ኦስሎ፣ኖርዌይ

No comments:

መንግስት ከዲፕሎማሲያዊ መፋዘዝ ይውጣ! የአረብ ሊግ በአባይ ግድብ አንጻር የወሰነውን የጸብጫሪነት ተግባር በውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር የምላሽ መግለጫ ብቻ የሚበቃ ሊሆን አይገባም።መንግስት ያልሰራው ግዙፍ ስራ ኢትዮጵያን ለአደጋ እንዳያጋልጣት ያሰጋል።

የኢትዮጵያ ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ዋና መስሪያቤት መንግስት በፍጥነት ሊሰራቸው የሚገቡት አምስት ወሳኝ ዲፕሎማሲያዊ ተግባራት ========= ጉዳያችን አለርት ========= የአረብሊግ አንዱ የሚታወቅበት መለያው እንደባዶ ቆር...