ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Thursday, January 30, 2014

አሜሪካ በኢትዮጵያ ጉዳይ ተነቃቃች …ወይንስ ?(አጭር ማስታወሻ)



አሜሪካ ዘግይታም ቢሆን በኢህአዲግ ላይ የምታደርገውን ድጋፍ ቀስ በቀስ ለመሳብ እያሰበች ይመስላል።በሳምንቱ ውስጥ አሜሪካ ለኢትዮጵያ የምትሰጠው እርዳታም ሆነ ድጋፍ የዜጎችን ከመሬታቸው መፈናቀል የሚያስከትል እንዳይሆን ቅድመ ሁኔታ እንዲኖረው መወሰኑ በተነገረ በቀናት ውስጥ የኢትዮጵያ መንግስት የሰብአዊ መብት ካላከበረ በቀር  ለፖሊስ እና ለጦር ኃይል ከአሜሪካ የሚሰጠው ድጋፍ በቅድመ ሁኔታ ስር እንዲሆን ወስኗል።

አሜሪካ  ይህንን ለማድረግ 23 አመታት ብትዘገይም ለዛሬው እርምጃ መጀመር ግን ምክንያቶቹ ከእዚህ በታች ከተዘረዘሩት የትኞቹ ይሆኑ?

1/ በድንገት ለኢትዮጵያ ሕዝብ ማሰብ ጀምራ?

2/ የቻይና በኢትዮጵያ መንሰራፋት ለአፍሪካም የተረፈ መሆኑ አስግቷት?

3/ ኢትዮጵያውያን በዋይት ሃውስ ደጃፍ ለአመታት ያደረጉት ሰልፍ በድንገት ትዝ ብሏት?

4/ የኢትዮጵያ ሕዝብ በኢህአዲግ አሰራር መማረሩን እና መቁረጡን ስላወቀች?

5/ የኢትዮጵያ ሁኔታ ወደባሰ መስመር የመሄዱ አዝማምያ ለአካባቢው አለመረጋጋት መዘዝ ስላለው የአካባቢ አረጋጊ ኃይል ላለማጣት?

6/ የድል አጥብያ አርበኛ ለመሆን?

መልሱ በሂደት የሚታይ ነው።

ላለፉት 23 አመታት ኢህአዲግ ሲታሰብ አሜሪካም አብራ ነበረች።ይህ ሀቅ ነው።ኢትዮጵያ የጎሳ ፖለቲካ ሲታወጅባት ጉዳዩ አደገኛ መሆኑን በትንሹ ለጎሳ ፖለቲከኛ መንግስት ስትናገር ብንሰማት ጥሩ ነበር። የሆነው ሆኖ የዛሬ የአሜሪካ መነቃቃት ደስ የሚል ነው።አሜሪካ ግን ተነቃቃች ማለት የሚቻለው ለኢትዮጵያ አንድነት፣የግዛት ሉአላዊነት እና የባህር በር ባለቤትነት የማያወላውል አቋም ስታሳይ ነው። ኢትዮጵያ ከፊቷ የሚጠብቁ ብዙ ጉዳዮች አሏት እና ዛሬ ማለት የሚቻለው አሜሪካ በርታ በይ ቀጥይ ገና ነሽ ይመስለኛል።

No comments:

ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።