ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Monday, January 13, 2014

''በ 21ኛው ክ/ዘመን ፕሮፓጋንዳ ሠርቶ፣ጥላቻ ዘርቶ ፖለቲካ እሰራለሁ በእዚህም እታመናለሁ የሚል ስብስብ ካለ ውጤታማ የሚሆን አይመስለኝም'' ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ለሕብር ራድዮ የሰጡት ቃለ-ምልልስ (ኦድዮ)



የብሔር መብት በተመለከተ ያላችሁ አስተያየት ምንድን ነው?


''የግለሰቦች መብት ከተከበረ የቡድን መብት ይከበራል።ባህሌ፣ቋንቋዬ፣እምነቴ  እኔ ውስጥ አለ። በቋንቋዬ መናገር የእኔ መብት ነው፣የሙያ ማኅበር መመስረት የእኔ መብት ነው።የእኔ መብት ያልሆነ የቡድን መብት አይኖርም።የግለሰብ መብት ከተከበረ የማይከበር የቡድን መብት የለም።የወለጋን ሕዝብ ለማስተዳደር ከጎጃም ማምጣት የለብንም።የፌድራል አስተዳደሮች የራሳቸውን ቋንቋ መምረጥ እንዳለባቸው የታወቀ ነው።ዛሬ የአንድ ሰፈር ሰው የሌላ ሰፈር ሰው የሚወክልበት ሁኔታ የለም።ይህንን ዘመን አልፈነዋል።

የአፄ ምንሊክን 100ኛ አመት መታሰቢያ በተመለከተ 


''አፄ ምንሊክ ለእዚህ ትውልድ አርአያ የሚሆኑ ብዙ ነገሮች አሉዋቸው።አፄ ምንሊክ መልካም መሪ አልነበሩም የሚሉ ካሉ መብታቸው ነው።እኛ እሳቸውን እየዘከርን ያለነው ለሀገር ግንባታ ባደረጉት መልካም ነገር ነው።ለአፍሪካ ሕዝብ ነፃነት ተምሳሌት በመሆናቸው እንዘክራቸዋለን።'ጡት ቆረጡ' እንደዚህ ነው እንደዛ ነው ብሎ በመናገር በ 21ኛው ክ/ዘመን ፕሮፓጋንዳ ሠርቶ፣ጥላቻ ዘርቶ ፖለቲካ እሰራለሁ በእዚህም እታመናለሁ የሚል ስብስብ ካለ ውጤታማ የሚሆን አይመስለኝም።'' ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት ለሕብር የሰጡት ቃለ-ምልልስ




ጉዳያችን GUDAYACHN BLOG

No comments:

መንግስት ከዲፕሎማሲያዊ መፋዘዝ ይውጣ! የአረብ ሊግ በአባይ ግድብ አንጻር የወሰነውን የጸብጫሪነት ተግባር በውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር የምላሽ መግለጫ ብቻ የሚበቃ ሊሆን አይገባም።መንግስት ያልሰራው ግዙፍ ስራ ኢትዮጵያን ለአደጋ እንዳያጋልጣት ያሰጋል።

የኢትዮጵያ ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ዋና መስሪያቤት መንግስት በፍጥነት ሊሰራቸው የሚገቡት አምስት ወሳኝ ዲፕሎማሲያዊ ተግባራት ========= ጉዳያችን አለርት ========= የአረብሊግ አንዱ የሚታወቅበት መለያው እንደባዶ ቆር...