Friday, February 12, 2021

የትግራይን ሕዝብ እንረዳለን።ትግራይን ለዛሬው ርሃብ ያደረሳት የኢትዮጵያ መንግስት ሳይሆን ኢትዮጵያን ሊበትን ሲሞክር የተበተነው ህወሓት እንደሆነም ጠንቅቀን እናውቃለን።

የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል መቀሌ የመድሃኒት አቅርቦት ሲያወርድ 

  • ከ20 ዓመታት በላይ ሲጠብቀው የነበረ ወታደር በተኛበት ከገደለ በኃላ ''የኤርትራ ወታደር ገባ'' የሚለው ድምፅም ህወሓት ትግራይን ለእዚህ እንዳበቃት ሲናገር መሰማት አለበት። 

በትግራይ ካለፈው ጥቅምት 24/2013 ዓም የህወሓት አመራር በኢትዮጵያ ጦር ኃይል ላይ ከፈፀመው ጥቃት እንዲፈፀም ትእዛዝ ከሰጠበት ጊዜ ጀምሮ (የቀድሞው ህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል አቶ ሴኮቱሬ እንዳረጋገጡት) የኢትዮጵያ የምድር እና የአየር ኃይል የሕግ ማስከበር ስራውን በአጭር ጊዜ ካጠናቀቀ በኃላ በውጭ ሀገር የሚኖሩ የህወሓት አባላት አስፋልት ላይ ከመተኛት እስከ የጎዳና ላይ ትያትር እየሰሩ ሲያሳዩ ሰንብተዋል።

የቀድሞው ህወሓት በትግራይ ሕዝብ እንደ የልጆች መጫወቻ 'ጢባጥቤ' ሲጫወትበት ዓመታትን አስቆጥሯል።ጥቂት ቅምጥሎች ፍርፋሪ  ለተከታዮቻቸው እየወረወሩ እነርሱ ከአዲስ አበባ እስከ ዱባይ፣አውሮፓ እና አሜሪካ ስንደላቀቁ የትግራይን ሕዝብ ከኤርትራ እስከ አፋር፣ከአማራ እስከ ሱማሌ ድረስ ብልግና፣ግፍ፣እና ዝርፍያ በተሞላ ተግባራቸው ከማጋጨታቸውም በላይ ግልጥ የሆነ የዘር ፍጅት ሊያስነሱበት አሲረዋል። ሆኖም ሀገሩ ኢትዮጵያ፣ሕዝቡም የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆነና በአስተዋይነት ሁሉንም  አለፈው።

አሁን በሕግ ማስከበሩ ሂደትን ተከትሎ በትግራይ ለምግብ እጥረት የተጋለጡ ቁጥራቸው ብዙ እንደሆነ የኢትዮጵያ መንግስት፣የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን እና የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ባወጡት የተለያዩ መግለጫዎች አስታውቀዋል።ለክልሉ ዕርዳታ የማሰባሰብ ስራም በአርቲስት እና አክቲቪስት ታማኝ የሚመራው የግሎባል አልያንስ፣በናትናኤል አስመላሽ የተደረገው እና አደባባይ ሚድያን ጨምሮ ያስተዋወቀው የጎፈንድሚ የገንዘብ ማሰባሰብ እና ሌሎችም እየተካሄዱ ነው። በውጤቱም በሚልዮን የሚቆጠር ገንዘብ እና በርካታ የምግብ እርዳታዎች ተገኝተዋል።እነኝህ ድጋፎች የአዲስ አበባ፣አፋር፣አማራ እና ሌሎች ክልሎች በራሳቸው እያሰባሰቡ ወደ ትግራይ የላኩት ጋር ሲደመር ችግሩን ለመቅረፍ የራሱ የሆነ አስተዋፅኦ ይኖረዋል።ይህም ሆኖ ግን አሁንም ተጨማሪ ዕርዳታዎች እንደሚያስፈልጉ ተነግሯል።በትግራይ ክልል ከአንድ ነጥብ አምስት ሚልዮን ሕዝብ በላይ በዘመነ ህወሓትም በምግብ ሴፍት ኔት የሚኖር እንደነበር የሰላም ሚንስትር በቅርቡ የክልሉን የግብርና መረጃ ጠቅሶ ማስታወቁ ይታወሳል።

ለማጠቃለል፣በትግራይ ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ ተከትሎ የኢትዮጵያ ሕዝብ በሚገባ ይረዳል።ላለፉት ሶስት ዓመታት ከጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ እስከ አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ፣ከጳጳስ እስከ ሙፍቲ፣ከሴቶች እስከ ወጣቶች ወደ መቀሌ ተጉዘው ጦርነት አይገባም፣በሰላም መነጋገር ብቻ ነው አማራጩ በሚል ህወሓት ተለምናለች።ህወሓት እና ጀሌዎቹ ግን ይህንን ሁሉ ልመና እረግጠው ከ20 ዓመታት በላይ በበርሃ ሆኖ የትግራይን ሕዝብ ሲጠብቅ የኖረውን ወታደር በተኛበት ከመግደል ልብሱን እያስወለቁ እስከማባረር ደረሱ።ለ27 ዓመታት በመላዋ ኢትዮጵያ ህወሓት ያፈሰሰችው ደም ሳይበቃት ከቤተሰቡ ለዓመታት ተለይቶ በትግራይ የሚንከራተተው  የመከላከያ ሰራዊት ላይ የግፍ ግፍ ፈፀመች።ዛሬ ይህንን ግፍ በትግራይ ባለው ረሃብ ለማረሳሳት የሚሞክሩ በትግራይ ለደረሰው ረሃብ መንግስትን እና የጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አመራርን ለመውቀስ ሲሞክሩ ትንሽ እፍረት አይሰማቸውም።መንግስት የሕግ ማስከበሩን ሥራ ባይሰራ ኖሮ መላዋ ኢትዮጵያን ኤርትራም ጭምር በደም ሊነክሩ እንደነበር የሚያውቅ ዜጋ ያለ አይመስላቸውም።አልቻሉም እንጂ ንፁሃን የባህርዳር፣ጎንደር እና አስመራ ነዋሪዎች ላይ ሮኬት ሲወረውሩ ዓላማቸው ንፁሃንን መፍጀት ነበር።ኢትዮጵያን ለመበትን ያልተሳካላት ህወሓት እራሷ ተበተነች። ስለሆነም የትግራይን ሕዝብ እንረዳለን።ትግራይን ለዛሬው ርሃብ ያደረሳት የኢትዮጵያ መንግስት ሳይሆን ኢትዮጵያን ሊበትን ሲሞክር የተበተነው ህወሓት እንደሆነም ጠንቅቀን እናውቃለን።ከ20 ዓመታት በላይ ሲጠብቀው የነበረ ወታደር በተኛበት ከገደለ በኃላ ''የኤርትራ ወታደር ገባ'' የሚለው ድምፅም ህወሓት ትግራይን ለእዚህ እንዳበቃት ሲናገር መሰማት አለበት። 
*******************

Thursday, February 11, 2021

የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በጎ ድራጎት ድርጅት በአዲስ አበባ የሚገኘውን የማኅተመ ጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታልን ወለደ።የጋንዲ መታሰብያ ሆስፒታል ትናንት አዲስ ''ልጅ'' ሆስፒታል ወለደ።(ሙሉ ፊልሙን ይመልከቱ)

ጉዳያችን /Gudayachn

በኢትዮጵያ የበጎ አድራጎት ታሪክ ስመ ጥሩ ድርጅት የነበረው የቀዳማዊ  አፄ ኃይለ ሥላሴ በጎ ድራጎት ድርጅት (የቀ.ኃ.ሥ ፋውንዴሽን) ነበር። የድርጅቱ ማቋቋሚያ ቻርተር በሐምሌ 15 ቀን 1951ዓ.ም በመንግሥት ማስታወቂያ ቁ. 253/51 መሠረት ወጥቶ፤ በየካቲት 21 ቀን 1952ዓ.ም በአዋጅ ቁጥር 261/52 መሠረት ፀድቋል። ድርጅቱ  ዘርፈ-በዙ ተግባራትን አከናውኗል። በሥሩም የቀ.ኃ.ሥ ሽልማት ድርጅትን፣ የአባድር እርሻ ልማትን፣ የቤተሳይዳ ቀ.ኃ.ሥ ሆስፒታልን (የዛሬው የካቲት 12 ሆስፒታል መሆኑ ነው)፤ የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታልን (ያኔ የዛሬው ክፍለ ሀገር አውቶቡስ ተራ ጋር ነበር)፤ የሐረር ልዑል ራስ መኮንን ሆስፒታልን (በተለምዶ ጀጉላ ሆስፒታል ይባላል)፤ በቅደስ ኡራኤል ቤተ-ክርስቲያን ጀርባ የነበረውን የቀ.ኃ.ሥ ዕጓለ ማውታ ትምህርት ቤትን፤ ስድስት ኪሎ የሚገኘውን የመርሐ ዕውራን ትምህርት ቤትን፤ የማኅተመ ጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታልንና ደብረ ሊባኖስ የሚገኘውን የቤተ ሰሊሆም (ጡረተኞች ቤት) የያዘ ነበር።

ዛሬ የካቲት 4/2013 ዓም የማኅተመ ጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታል በአንድ ጊዜ ሰባት እናቶችን በተመሳሳይ ሰዓት ቀዶ ጥገና ማድረግ የሚችል አገልግሎት የያዘ ዘመናዊ ሆስፒታል ወልዷል።ለዝርዝሩ ይህንን የፋና የቀጥታ ስርጭት ይመልከቱ።
============
ማስታወቂያ 
============
በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ ሂሳብ ሊሞሉ እንደሚችሉ ያውቃሉ? 

አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ - 

Thursday, February 4, 2021

Why are Global Institutions,Governments and Media 'misleading’ on the current situation of Tigray Region in Ethiopia?

*********************

By Getachew Bekele Damtew

Gudayachn Editor 

February 5,2020

********************

The global community is in a ‘confusing’ position, in case of Ethiopia's current situation in the Tigray region. Denial of law enforcement measures taken by the federal government and taking it as it was to attack the region’s residents, are the day-to-day talk of the former Tigray People Liberation Front (TPLF) propagandist machines in abroad.On the other side,no one is considering, how the horn of Africa and perhaps the rest of Africa could be affected, if TPLF was continuing on its de facto power. In the last three months,the federal government of Ethiopia Defence Force and the people have sacrificed, not only to save the unity of Ethiopia but to safeguard the peace and stability of the horn of Africa.How ever, this fact is not well understood by International Institutions,Governments and Media.

 

There are two points raised from the global community.One, access to aid to Tigray region is not sufficient and two, there are humanitarian crises in the region.Both questions have approaches differences and 'clear' paradox.Because both questions have disregarded the Ethiopian government's replies through its different organs including the Prime Minister office,spokesman of the Ministry of Foreign Affairs and Ministry of Peace press releases.


According to the Ministry of Peace latest press release, the government provision of humanitarian Aid reached 1.6 Million to the Tigray region of Ethiopia.Yesterday,the Minister of Peace, Muffriat Kamil,briefed the Walta Information Center on the ongoing humanitarian and rehabilitation work in the region. Following the implementation of the law enforcement, the Minister said, more than 305,000 quintals of food aid has been provided to 1.6 million people in Tigray region. Non-governmental organizations (NGOs) have also been involved in the process, she said, in addition to 22,000 metric tons of grain, 69,000 metric tons of grain are in the process of being delivered to the safety net.


The minister also said the Tigray region has been without electricity, telecommunications and banking services since the end of the law enforcement operation in the region.However, a great advancement is made on returning back electricity,tele and banking service.The government efforts have been made also to supply the drug at a cost of 71 million birr.The minister’s briefing also indicated as there are 92 humanitarian aid centers in Tigray Region at this particular time.If we included the refugee centers the numbers have been able to reach 80 centers.


At the end of last week,the UNHCR higher commissioner, Filippo Grandi has been on work visit to Tigray region together with the minister of Peace and deputy PM and FM Demeke Mekonen.Regarding this particular high level visit with UNHCR high commissioner, Minister of Peace Muffriat Kamil shared her feeling in amharic on her social media translated by Gudayachn as follows : -

''I had the opportunity to spend time with the UN High Commissioner for Refugees (UNHCR) and other government officials at a refugee camp in the Tigray region.Seeing them in the middle of their lives gave me strength and hope. We discussed with the representatives of the shelters community, including representatives of women, children, youth and religious leaders at the Hadi Harush and Mai Aini shelters on the provision of basic services and social issues that need to be improved.I have had the opportunity to understand the positive performances and shortcomings of the camps, so that we can further improve our service. We are aware that more than 70 percent of the refugees are in good condition in both camps. We will continue to strengthen the reforms we have begun since 2011 based on the fact that the remaining two camps are below the standard of international camp formation and are not conducive to living.It has recently brought more than 3,000 refugees to Hadi Harush and Mai Aini camps, and we will continue to do so. Together, we work day and night to ease the problems of our people, further strengthening our good experiences and folding values.''


All the above heading news on Tigray region of Ethiopia were not properly broadcasted or reported on International Media.Therefore, top policy makers, parliament members and even prime ministers of Europe and USA were not able to obtain the necessary information from their own country’s media. This is a huge crises of information.Here,we need to get the necessary answer for a critical question of Why are  Global Institutions,Governments and Media misled on the current situation of Tigray Region in Ethiopia? 


The answer is not so complicated. It is because the pre-established former Tigray People Liberation Front (TPLF) structure abroad reacted to cheat the global community intentionally.For this purpose, thousands of Twitter accounts were opened in the last four months.


On November 17/2020, Washington Post, has confirmed the above statement as follows: -Twitter data collected from Nov. 1 to 10 (2020) showed that 30 percent of tweets about Tigray and Abiy were from accounts created this year. Nearly half (47 percent) of these tweets were from accounts created in late October and early November. After Nov. 4, the number of new accounts created per day grew from an average of 21 to 245. Their tweets are overwhelmingly (although not exclusively) anti-government.”


November 4/2020 was the second date since TPLF militia has opened fire on Ethiopian National Defence Force (ENDF) in Tigray region.Investigative reports from the Federal Police of the Federal Government shows that the former TPLF  'personnel' was getting ready for over two years to recapture the central political power of Ethiopia. Therefore the 'abroad wing' of TPLF was aware to start the social media campaign against the Federal Government of Ethiopia. Financial and Human resources were allocated a year back.The plan was to launch the social media campaign as soon as the militia opened fire against the Federal Army in Tigray region. In short, this was the process and result of how the flow of fake news controlled the global media including Reuters and BBC correspondents and editors. This is a typical case for the failure of global media in the 21st century.


Last but not least,all fake news reported by globally dominant media reported on the law enforcement process of the Federal Government of Ethiopia, need to be checked and exposed to the International  community.Because these are the typical cases for the study of Journalism at the University level.Majority of Ethiopians,both abroad and at home, have already lost their confidence on international Media of the west. All  these happened after the pro-TPLF fake reports were magnified and reported  by the western media. The biased-western media is not only serving as the 'propaganda machine' for the former TPLF's foreign wing.The western media is not only focused on the Tigray region humanitarian issues.It has also opened full of negative campaign against the Ethiopian Government law enforcement process in Tigray and the PM Abiy Ahmed (PhD) personal integrity.I think such a kind of situation may have a short and long time consequences on the relationship between the west and the very strategic land of the horn of Africa,Ethiopia. Ethiopians both in Addis and Washington D.C are discussing the main cause of the western media's incapability to check and balance fake news produced and released from the 'TPLF foreign wing' on the current situation of the Tigray region in Ethiopia. In fact,it is not possible to say that the western media has only fully owned fake-news due to the TPLF foreign wing social media campaign.Because unless the western media and their foreign policy makers ignored the fact news, they could not be cheated on such a huge level. It is not less than shame.


Getachew Bekele Damtew

e-mail= getachewb221@gmail.com


============
 Advertisement/ ማስታወቂያ
============

Fetan Top up mobile click the below link 

አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ - 



መተማ ላይ ለኢትዮጵያ እና ለሰንደቅ ዓላማዋ የፈሰሰውን የአፄ ዮሐንስ 4ኛን ደም ለረገጡ ፍርዱ አይዘገይም!

ጉዳያችን/Gudayachn

ኢትዮጵያ ዛሬ ላይ የደረሰችው ብዙዎች መስዋዕት ከፍለውላት ነው።መስዋዕትነቱ ከተራ ገበሬ እስከ ነገስታቶቿ እራሳቸውን ሰጥተው፣ደማቸውን አፍስሰው እስካሁን አስጠብቀው አስረክበውናል።ለኢትዮጵያ ሰማዕት ከሆኑት ውስጥ አፄ ዮሐንስ አራተኛ አንዱ ናቸው።የሸገር ኤፍ ኤም ጋዜጠኛ እሸቴ አሰፋ ከሶስት ዓመታት በፊት የአፄ ዮሐንስን እረፍት አስመልክቶ በሰራው የራድዮ ፕሮግራም ላይ እንዲህ አለ -

''በ1881 ዓም የኢትዮጵያ ንጉሰ ነገስት አፄ ዮሐንስ በወረራ መተማንና አልፎም እስከ ሳር ውሃ ተቆጣጥሮ የነበረውን የሱዳን ሰራዊት ለመዋጋት ወደ መተማ ዘመቱ፡፡አፄ ዮሐንስ ወደ መተማ ሰራዊታቸውን አስከትለው የሄዱት፣ ሰሃጢ ላይ ከጣሊያኖች ጋር የነበራቸውን ፍጥጫ ትተው ነው፡፡መጋቢት 1 ቀን ጠዋት ጦርነቱ ተጀመረ፡፡ አፄ ዮሐስን ራሳቸው እንደ አንደ አንድያ ወታደር ሆነው በጦር ግንባር ገብተው ተዋጉ፡፡በጦርነቱም የኢትዮጵያ ሠራዊት ድል ለማድረግ በተቃረበበትና የሱዳን ሠራዊት ከምሽጉ ወጥቶ ለመሸሽ በተዘጋጀበት ወቅት አፄ ዮሐንስ እጃቸው ላይ ቆሰሉ፡፡ ቢሆንም ከጦርነቱ መካከል አልወጡም፡፡እንደገና በግራ እጃቸው አልፋ ወደ ደረታቸው የዘለቀች ጥይት መታቻቸው፡፡ አጃቢዎቻቸው ወደ ድንኳናቸው ወሰዷቸው፡፡

አፄ ዮሐንስ በመቁሰላቸው ምክንያት በማግስቱ መጋቢት 2፣ 1881 ዓ.ም አረፉ፡፡የኢትዮጵያኖቹን መሸሽ ያየው የሱዳን ሰራዊት እግር በግር እየተከታተለ ማጥቃቱን ቀጠለ፡፡የአፄ ዮሐንስን አስከሬን ድንኳንም ከበበው፡፡ታላላቅ የጦር መኮንኖቻቸውና በርካታ ታማኝ ሰራዊታቸውም የጌታችንን አስክሬን አናስማርክም እያሉ ፅኑ ውጊያ አደረጉ፡፡ብዙዎችም በአስክሬናቸው ዙሪያ ረገፉ፡፡በመጨረሻ የደርቡሽ ጦር ድል አድርጐ፣ የአፄ ዮሐንስን አስክሬን ማረከ፡፡ አንገታቸውንም ቆርጦ ካርቱም ገበያ ላይ አዞሩት፡፡የአፄ ዮሐንስ ሰራዊት የሞተው ሞቶ የተማረከው ተማርኮ የቀረው ወደ ደጋው አፈገፈገ፡፡ምንም እንኳ አፄ ዮሐንስ ሞተው ሰራዊቶቻቸው ተበታትኖ ደርቡሾች ጊዚያዊ ድል ቢያገኙም የኢትዮጵያን መሬት ይዘው ለመቆየት አልቻሉም፡፡

አፄ ዮሐንስ አንገታቸውን የሰጡላት ኢትዮጵያም በነፃነት እስከ አሁን ኖራለች፡፡'' አሰፋ እሸቴ ሸገር ራድዮ መጋቢት 2፣2009 ዓም 


ይህ ዓመት አፄ ዮሐንስ ለኢትዮጵያ ክብር እና ለሰንደቅ ዓላማዋ ከተሰዉ 132 ዓመታቸው ነው።አሁን ባለንበት ዘመን የኢትዮጵያ ፍቅር ሳይሆን የድርጅት ፍቅር ያሰከራቸው የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ በዓለም አደባባይ ክደው የህወሓትን ዓርማ እንደ የሀገር ዓርማ ይዘው በእየአደባባዩ የሚሰለፉት ለኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ደማቸው የፈሰሰውን የአፄ ዮሐንስን ደም የረገጡ ናቸው።ይህ ብቻ አይደለም ኢትዮጵያን ከመካድ በላይ የአፄ ዮሐንስን አንገት ቆርጠው ካርቱም ላይ ካዞሩት ጋር ወግነው ኢትዮጵያን ለመውጋት ሲያደቡ ማየት ምን ዓይነት ክህደት በኢትዮጵያ ላይ እየተፈፀመ እንደሆነ ያመላክታል።

የአፄ ዮሐንስ ደም ላይ የሚረማመዱቱ የዛሬዎቹ ቅምጥሎች በኢትዮጵያ የጦር ሰራዊት ላይ የእልቂት ድግስ ደግሶ ጥቅምት 24/2013 ዓም በተኛበት ሊፈጀው የሞከረውን እና ኢትዮጵያን ለባዕዳን አሳልፎ ለመስጠት የተደራደረውን ህወሓት በኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ቀይረው ኢትዮጵያን በዓለም አደባባይ ይሰድቧት ይዘዋል።ለነገሩ ፊታቸው ያብለጨለጨው፣ባዕዳንም ያከበሯቸው ለዘመናት አባቶቻቸው በተሰዉላት ሰንደቅ ዓላማ ነበር።ዛሬ በአደባባይ ክደዋት ''ኢትዮጵያዊ አይደለንም'' እያሉ ተዘባበቱባት እንጂ። ''ከተራበ ለጠገበ አዝናለሁ'' እንዲሉ አሁን በእየውጭ ሀገሩ የአፄ ዮሐንስን ደም የነጠበባትን ሰንደቅ ዓላማ እየጣሉ የድርጅት ጨርቅ ይዘው የሚንገላወዱት እና ህዝብን ለማታለል የሚሞክሩት በትግራይ ሕዝብ ስም በመነገድ ነው።በየትኛውም የዓለም ክፍል ጦርነት ካለ ረሃብ እና የህዝብ መፈናቀል ይከተላል።ይህ የሚያሳዝን ታሪክ ነው።በትግራይ የደረሰውም ረሃብም ሆነ የህዝብ መፈናቀል ያሳዝናል።የኢትዮጵያ ሕዝብም ሆነ መንግስት ቀን ከሌት ተረባርቦ አስፈላጊው ዕርዳታ እንዲደርስ እያደረገ ነው።በኢትዮጵያ ሕዝብ ገንዘብ ወደ ውጪ የሄዱት ኢትዮጵያን መካዳቸውን በአደባባይ የተናገሩቱ ግን አንዲት ሳንቲም ለትግራይ ሕዝብ ስልኩ አልታዩም።ይልቁንም አፄ ዮሐንስ የሞቱላትን ሰንደቅ ዓላማ  ክደው የፈሰሰውን ደማቸውን ሲረግጡ እየታዩ ነው። መተማ ላይ ለኢትዮጵያ እና ለሰንደቅ ዓላማዋ የፈሰሰውን የአፄ ዮሐንስ 4ኛን ደም ለረገጡ ፍርዱ አይዘገይም! 
=====================///=============
ድምፃዊ ፀሐዬ ዮሐንስ ኢትዮጵያ!


============
ማስታወቂያ 
============
በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ ሂሳብ ሊሞሉ እንደሚችሉ ያውቃሉ? 

አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ - 

 

Monday, February 1, 2021

ኢትዮጵያን የመክበብ እና የማዋከብ ሙከራን ለማክሸፍ



ኢትዮጵያ ያለችበትን ቁልፍ አቀማመጥ ብቻ ሳይሆን ከሱዳን እስከ ጂቡቲ ከየመን እስከ ሳውዲ ያለው በረሃማ መሬት ጋር ሲነፃፀር  ምድረ ገነት ነው።እነኝህ በደረቃማ መሬት ላይ ተፈጥሮ ያሰፈረቻቸው አንዳንድ መንግሥታት የአሁኑም ሆነ መጪው  ትውልዳቸውን የሚያጠጡትን ውሃ ለማግኘት ዙርያቸውን ሲያማትሩ ዓይናቸውን የጣሉት ኢትዮጵያ ላይ ነው።ከእነኝህ አማታሪዎች ውስጥ የመካከለኛው ምስራቅ ጋዜጦች እንደ ''አል-አረቢያ'' ያሉት ጋዜጦች የኢትዮጵያን ዓባይ ወንዝ ''የአረቡ ዓለም ወንዝ'' እያሉ ሲፅፉ ትንሽም 'ስቅ!' አላላቸውም።ይሄው ጋዜጣ ባሳለፍነው ክረምት ኢትዮጵያ የአባይን ወንዝ መገደቧ የአረቡን ዓለም ለመቆጣጠር ነው እና የአረብ ሀገሮች በሙሉ ሊነሱ ይገባል  ሲሉ የአረብ ሊግ ቁንጮ መናገራቸውንም አስነብቦናል።

የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ፍላጎት ግልጥ ነው።ኢትዮጵያ እንድትነሳ አለመፈለግ ብቻ ሳይሆን ከፋፍለው ሊቆጣጠሯት እያለሙ ይቃዣሉ።ይህንን ህልማቸውን ደግሞ ኢትዮጵያ የውስጥ ሁከት የገባች በመሰላቸው ጊዜ ሁሉ እና የዓለምም ሆነ የመካከለኛው ምስራቅ ትኩረት በተደናበረበት ጊዜ  ኢትዮጵያን ለመቆጣጠር ያልሞከሩበት ጊዜ የለም።የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች በኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ በመግባት ቢያንስ ላለፉት ሃምሳ ዓመታት ውስጥ ብቻ በርካታ ሴራዎችን አሴረዋል። የኢትዮጵያ እና የኤርትራም ሆነ የህወሓት 17 ዓመታት ጦርነት ብንመለከት ከገንዘብ እስከ ቁሳቁስ  ከፍተኛ ድጋፍ ያገኝ የነበረው ከመካከለኛው ምስራቅ እና ሱዳን መንግሥታት ነበር።ለእዚህም ነው ''የኤርትራ ጉዳይ'' የተሰኘው መፅሐፍ ፀሐፊ ክቡር አምባሳደር ዘውዴ ረታ ''የኤርትራን ጉዳይ  እግሩ ኢትዮጵያ ይሁን እንጂ  ራሱ ያለው ውጪ ነው'' ያሉት።ዛሬ የኢትዮጵያ እና የኤርትራ መቀራረብ ያስደነገጣቸው የኢትዮጵያ የቅርብም ሆኑ የሩቅ ጠላቶች ዋና ስጋት ኢትዮጵያ ወደ ቀይ ባሕር የመውጣት ሂደት እና ይህንኑ ባሕርም ሆነ የኢትዮጵያን የተፈጥሮ ሀብት የመቆጣጠር ህልማቸው ከንቱ እንደሚሆን ከወዲሁ ስላወቁ አርበትብቷቸዋል።

በሌላ በኩል የአፍሪካ የተፈጥሮ ሐብት መተዳደሪያቸው የሆኑ አደጉ የሚባሉ ሐገሮች የኢትዮጵያ መነሳት እንደ እነርሱ አባባል ''መንሰራራት'' እንደ አንድ ስጋት ይመለከቱታል።ይህ ደግሞ ከሁለት ምክንያቶች ይመነጫል።አንዱ፣ኢትዮጵያ ለሌሎች የአፍሪካ ሀገሮች ምሳሌ ሆና ሌሎች የአፍሪካ ሀገሮች እጅ አዙር ቅኝ አገዛዝን ለማንኮታኮት እንዳይነሱ ሲሆን።ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ በኢትዮጵያ ላይ ካላቸው የተፈጥሮ ሀብት፣ማዕድናት እና ጅኦ-ፖለቲካዊ ስልት አንፃር የኢትዮጵያን ፖለቲካዊ፣ወታደራዊ እና ምጣኔ ሃብታዊ ጉዳዮች ሁሉ በእጅ አዙር ለመዘወር ከመፈለጋቸው የተነሳ ነው።ለእዚህም ነው ኢትዮጵያን ለሃያ ሰባት ዓመታት በጎሳ ከፋፍሎ እርስ በእርስ ሲያናክስ አንዳች ያልተናገሩ መንግሥታትም ሆኑ የውጭ መገናኛ ብዙሃን፣የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በሚያስደንቅ ፍጥነት ካስወገደው በኃላ ታላቅ ድንጋጤ እንደፈጠረባቸው መደበቅ አልቻሉም።

ይሄውም የስልት መወናበድ እና መደናበር ስለፈጠረባቸው የሚይዙትን እና የሚጨብጡትን አሳጥቷቸው ሲወዛገቡ ታዝበናል።በእዚህም ምክንያት የግፈኛው የቀድሞው ህወሓት ደጋፊዎችም ሆኑ የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች አሁን ያላቸው ብቸኛ እና ቀሪ አቅም የሐሰት ወሬ በኢትዮጵያ እና በኢትዮጵያ መንግስት ላይ ማሰራጨት ሆኗል።በኢትዮጵያ እና በኢትዮጵያ መንግስት ላይ የሐሰት ዜና የማሰራጨቱን ሥራ እየሰሩ ያሉት ደግሞ በዓለም ላይ ስም አላቸው የሚባሉ ዓለም አቀፍ የዜና ማሰራጫዎች ጭምር እጅግ በሚያሳፍር ሁኔታ ከእውነት የራቁ ዜናዎች ሲያሰራጩ ሰንብተዋል።በእነኝህ የዜና ስርጭቶች ዙርያ የኢትዮጵያ የከፍተኛ ትምህርት ተማሪዎች የዜናዎቹን ሐሰትነት በሚያጋልጥ መንገድ የጥናት ፅሁፎቻቸውን ማቅረብ አለባቸው። ይህ የዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን የሐሰት ዜና ኢትዮጵያን የመክበብ ቁጥር አንድ ሙከራ መሆኑን ማወቅ ይገባል።

ሁለተኛው ኢትዮጵያን የመክበብ ግብ ይዞ ወደ ኢትዮጵያ ክልል የገባው የሱዳን ሰራዊት ነው።ሱዳን በቅርቡ በተጣደፈ መልኩ የትራምፕ አስተዳደር በሀገሪቱ ላይ ተጥሎ የነበረውን የዕቀባ መጣል ማንሳቷ ይታወሳል።ይህንን ተከትሎ ከአሜሪካ የገንዘብ ድርጅት ብድር ማግኘቷ እና ከግብፅ ደግሞ የአይዞሽ ባይ ምልክት መታየቱ ነው።ይህ በሱዳን በኩል የታየው ኢትዮጵያን የመክበብ ተግባር መልኩን ቀይሮ ነገ ከኢትዮጵያ ምሥራቅም ሆነ ምዕራብ በሌሎች ከኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ጋር የሚናበቡ ኃይሎች ተመሳሳይ ከበባ አያደርጉም ብሎ አለማሰብ አይቻልም።ይህ በእንዲህ እያለ የከበባዎቹ ዋና ኃይል አድርገው የሚወስዱት የኢትዮጵያን ውስጣዊ ሰላም ማተራመስ ነው።ኢትዮጵያን ለማተራመስ ደግሞ ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ስደተኞችን ሳይቀር ለመጠቀም የኢትዮጵያ ጠላቶች ማቀዳቸው አይቀርም።ኢትዮጵያ ወደ 1 ሚሊዮን የሚጠጉ ወደ ሃያ የሚሆኑ ሀገራት ስደተኞች መጠጊያ ናት።ስደተኞቹ በተለያዩ የሀገሪቷ ክፍል ስደተኛ መጠለያ ጣቢያ ውስጥ የሚገኙ ሲሆን ከዚህ በተጨማሪ ከፍተኛ ደረጃ የደረሰ የህክምና ችግር ፣ ከነበሩበት ሀገር በተለያዩ ጦርነቶች አልፈው ወሲባዊ ጥቃት ደርሶባቸው ለአዕምሮ ህመም የተጋለጡ እንዲሁም ጥበቃ የሚያስፈልጋቸውም በከተማ ስደተኝነት ተመዝግበው አዲስ አበባ ይኖራሉ።

ለማጠቃለል ኢትዮጵያውያን የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶችን የከበባ ሙከራ ለመስበር መንቀሳቀስ አለባቸው።የመጀመርያው የከበባ ሙከራ በዓለም አቀፍ የመገናኛ ብዙሃን የተፈፀመ ነው።ይህንን የሐሰት ዜና በኢትዮጵያ እና በኢትዮጵያ መንግስት ላይ የሚዘሩትን ምሑራን ባገኙት ቀዳዳ ሁሉ ተጠቅመው ምላሽ መስጠት ብቻ ሳይሆን የሕግ ማስከበር ሂደቱ ባይካሄድ ኖሮ ኢትዮጵያን ብቻ ሳይሆን የምስራቅ አፍሪካን በከፍተኛ ደረጃ ሊያበጣብጥ የሚችል ሁኔታ ሊፈጠር እንደሚችል የሚያስረዱ በርካታ ፅሁፎች፣ገለጣዎች እና የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ስራዎች በሰፊው መስራት ያስፈልጋል።በእዚህ በኩል በመላው ዓለም የሚገኙ የኢትዮጵያ ምሑራን መፃፍ በሚገባቸው ያህል ፅፈዋል ማለት አይቻልም።ኢትዮጵያ ያስተማረቻቸው ልጆቿ ለእዚህ ጊዜ ካልሆኗት ለመቼ ሊሆኗት ነው? ኢትዮጵያ በሐሰት ወሬ ይህንን ያህል ከበባ ሲፈፀምባት እንዳላዩ ማየት የት የተማርነው ሙያ ይሆን? በጦር ኃይል በኢትዮጵያ ክልል ውስጥ ወረራ የፈፀመው የሱዳን ሰራዊት የኢትዮጵያ ጦር ባልተጠበቀ ሰዓት እርምጃ እንደሚወስድበት ሳይታለም የተፈታ ነው። የሐሰት ወረራ የተከፈተባት ኢትዮጵያ ላይ የአፀፋ ምላሽ መስጠት ግን የእንግሊዝኛ ፊደል የቆጠረው ከሀገር ቤት እስከ ባሕር ማዶ የሚኖረው የኢትዮጵያ ምሑር ነው።ስለሆነም ምሑሩ ከትዊተር እስከ ዓለምቀፍ መገናኛ ብዙሃን በኢትዮጵያ ላይ እየተፈፀመ ያለውን ከበባ እና የማዋከብ ተግባር  ሰብሮ ለመውጣት ለኢትዮጵያ የሚቆምበት ጊዜ አሁን ነው።ኢትዮጵያ ግን ዛሬም ትጣራለች ምሑሩ የት ነው?
==========////==============
============
ማስታወቂያ 
============
በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ ሂሳብ ሊሞሉ እንደሚችሉ ያውቃሉ? 

አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ - 

Friday, January 29, 2021

ዓለም አቀፍ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋኅዶ ቤተ ክርስቲያን ምዕመናን መድረክ "ድምፃችንን ለቤተ ክርስቲያናችን" በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀ የውይይት መድረክ እሁድ ጥር 23/ 2013ዓም (Sunday January 31/2021 ዓም) በዙም አዘጋጅቷል።

ጉዳያችን/Gudayachn

ዓለም አቀፍ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋኅዶ ቤተ ክርስቲያን ምዕመናን መድረክ "ድምፃችንን ለቤተ ክርስቲያናችን"   በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀ የውይይት መድረክ እሁድ ጥር 23/ 2013ዓም   (Sunday January 31/2021 ዓም) በዙም አዘጋጅቷል። በዝግጅቱ ላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋኅዶ ምዕመናን ስለ ቀጣዩ ምርጫ ምን ያስባሉ? ሚናቸውስ ምንድን ነው ? ለእነዚህና ተመሳሳይ ጉዳዮች የሚነሱበት መርሐግብር እንደሆነ ከመርሃግብሩ ማስታወቂያ ለማወቅ ተችሏል። 

በዝግጅቱ ላይ ምሑራን ገለጣዎች የሚያቀርቡ ሲሆን በሀገር ቤት እና በመላው ዓለም የሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋኅዶ ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ካህናት፣ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት እና ምዕመናን እንደሚገኙበት ጉዳያችን ተረድታለች።
የስብሰባውን የዙም መግቢያ ኮዱን ከእዚህ በታች ካለው የመርሐግብሩ ፖስተር እና በድምፅ ከተለቀቀው ቪድዮ ላይ ማግኘት ይችላሉ።

============
ማስታወቂያ 
============
በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ ሂሳብ ሊሞሉ እንደሚችሉ ያውቃሉ? 
አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ - 


Wednesday, January 27, 2021

ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ ወጣት ዲና (Dina) በመጪው ቅዳሜ በኖርዌይ ቴሌቭዥን ለመሎዲ ግራንድ ፕሪክስ ውድድር ትቀርባለች።በስልክዎ ድምፅ በመስጠት እንድታሸንፍ ያድርጉ።

Etiopisk-norske, Dina Matheussen, er blant fire artister for Melodi Grand Prix.

በኖርዌይ ነዋሪ የሆነችው ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ ወጣት ዲና (Dina) ከአዲሱ ነጠላ ዜማዋ ላይ የተወሰደ ፎቶ 


ጉዳያችን/Gudayachn

ዲና ማቴዎስ ትባላለች።ነዋሪነቷ በኖርዌይ የሆነና ትውልደ ኢትዮጵያ የሆነች የ17 ዓመት ወጣት ነች።ገና 12 ዓመት እያለች ነው የዳንስ እና የድምፃዊነት ስራዋን የጀመረችው።ዲና የሙዚቃ ሰው ብቻ አይደለችም።በካራቴ ስልጠና ባለ ጥቁር ቀበቶ ተሸላሚም ድንቅ ወጣት ነች።

በ2014 ዓም እኤአ በኖርዌይ ቲቪ ቻናል 2 ላይ በሚቀርብ የኖርዌይ ታለንት ውድድር ላይ ከፍተኛ አድናቆትን አትርፋ ነበር።በ2017 ዓም በኖርዌይ ብሮድካስት ኮርፖሬሽን (ኤንአርኮ) የዓመቱ የዳንስ ውድድር ላይም ተሳትፋ ነበር።ባለፈው ዓመት በኖርዌይ አይዶል 2020 ላይ የበዮንሴን "Run the World (Girls)" የተሰኘውን ሙዚቃ በማቅረብ የኖርዌይ አድናቂዎቿን አስደምማለች።በ2019 ዓም በኖርዌይ ብሮድካስት ቴሌቭዥን (ኤንአርኮ) ቻናል 3 ላይ ''አንድ ነን'' ''we are one'' በሚል ያቀረበችው ሙዚቃ ላይ የት መጣ መሰረቷ ኢትዮጵያ መሆኑን በመድረኩ ላይ አሳይታበት ተመልካቾችን ሁሉ አስደንቃለች።

የዲና ተግባራት እነኝህ ብቻ አይደሉም።በእየዓመቱ ወደ ኢትዮጵያ እየሄደች የኦቲዝም እና ልዩ ልዩ ችግር ያለባቸውን ልጆች ለእዚሁ ሥራ ብላ ባጠራቀመችው ገንዘብ ትረዳለች።በያዝነው ዓመት ወደ ኢትዮጵያ ለተመሳሳይ መልካም ተግባር መሄድ ያልቻለቸው በኮቪድ ወረርሽኝ ሳብያ ነው።አሁንም ግን ኢትዮጵያውያንን ለመርዳት ገንዘብ እያጠራቀመች እንደሆነ እና መርዳቷን እንደምትቀጥል በያዝነው ሳምንትም ባደረገችው ቃለ መጠይቅ ገልጣለች።

ከዲና ጋር ያለፉት ሌሎች አራት አርቲስቶች ካርሰን (Karsten)፣ኤሚ (Emmy) እና ኡለ ሀርዝ (Ole Hartz)
FOTO: JULIA MARIE NAGLESTAD / NRK

ዲና የአሁኑ ቅዳሜ ጥር 22/2013 ዓም (ጃንዋሪ 30/2021ዓም) የኖርዌይ ብሮድካስት ቴሌቭዥን የኖርዌይ ሜሎዲ ግራንድ ፕሪክስ (Norsk Melodi Grand Prix) ውድድር  ከተመረጡት አራቱ ውስጥ ገብታለች።በውድድሩ ሰዓት ዲና እንድታልፍ ኢትዮጵያውያን በስልክ በሚሰጠው ድምፅ በመስጠት ተሳታፊ እንዲሆኑ ተጠይቀዋል።የኖርዌይ ቴሌቭዥን (ኤን አር ኮ -NRK) ''ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ ዲናዬ በዘፈኗ ውስጥ የአማርኛ ቃላት እንዲገቡ ያደረገችው መነሻዋ ከኢትዮጵያ መሆኑን ለማመልከት ነው'' በማለት ገልጦታል።

ዲና የቅዳሜውን ውድድር አልፋ ለፍፃሜው ስትደርስ በአውሮፓ ደረጃ ለሚደረገው ዋናው ውድድር ደረሰች ማለት ነው።በእዚህም አንዲት ትውልደ ኢትዮጵያዊት ለአውሮፓ ምርጥ ውስጥ ስትገባ የመጀመርያዋ ያደርጋታል ማለት ነው።በመሆኑም በቅዳሜው ምሽት ውድድር ላይ ኢትዮጵያውያውያን፣ትውልደ ኢትዮጵያውያን እና ኖርወጅያውያን ለዲና በስልካችሁ ድምፅ በመስጠት ኃላፊነታችሁን መወጣት አትዘንጉ።

ከእዚህ በታች ዲና ከሦስት ቀናት በፊት የለቀቀችውን ነጠላ ዜማ ከዩቱቧ ላይ ያለውን ከስር ይመለከቱ።


============
ማስታወቂያ 
============
በአንድ ደቂቃ ውስጥ በሀገር ቤት የሚኖር የቤተሰብ ወይንም የወዳጅዎን ስልክ ሂሳብ ሊሞሉ እንደሚችሉ ያውቃሉ? 
አገልግሎቱን ለማግኘት ከስር ሊንኩን ይጫኑ - 

The Ethiopian Orthodox Tewahedo Church is in turmoil in Athens, Greece.

His Holiness Abune Mathias I, Patriarch of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church, met with Greece's Ambassador to Ethiopia, Antonios Sg...