ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Sunday, January 29, 2023

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በተመለከተ ዛሬም ወሳኙ ጉዳይ ውስጣዊ አስተዳደራዊ መዋቅሯን ማዘመን አና ማቀላጠፍ ነው።የውጪው ፈተናዋ አስከምፅአት ቀን ድረስ የሚኖር ነው።(የጉዳያችን የዛሬም ጩኸት አንድ ነው!)


  • የዛሬ አስር ዓመት ምን ይገጥመናል ብሎ መፃፍ አና ዛሬ ይሄ ሆነ ሲባል ስሜትን በቁጣ አየገለፁ መናደድ ይለያያሉ።ጉዳያችን የዛሬው ቀን እንደሚመጣ ከአስር ዓመታት በላይ ጽፋለች።የጽሑፎቹን ሊንኮች ከስር ያገኛሉ።

  • አሁን ያሉት ቤተክርስቲያንቱን የመግፋት ድርጊቶች ችግር ብቻ ሳይሆን ያለው ለቤተክርስያንቱ ዕድል ይዞ የሚመጣ መልካም አጋጣሚም ነው።

======

ጉዳያችን 

====== የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን በምእመናኖቿ ብቻ ሳይሆን በስርጭትም ሆነ በማኅበራዊ አና ምጣኔ ሃብታዊ መለኪያዎች በኢትዮጵያ ግዙፍ አካል ነች። ይህንን እውነታ መጋፋቶች መሬት ላይ ያለውን አውነታ መቀየር አይቻልም።አሁን ያሉት ቤተክርስቲያንቱን የመግፋት ድርጊቶች ችግር ብቻ ሳይሆን ያለው ለቤተክርስያንቱ ዕድል ይዞ የሚመጣ መልካም አጋጣሚ ነው።የቤተክርስቲያኒቱ አስተምሮ ላይ ያሉ ግንዛቤዎች በአዲሱ ወጣት ትውልድ ዘንድ መደናበር የለም።ወዴት መሄድ አለብን፣አንዴት ቤተክርስቲያንን አናልማ ውዥንብር የለም።የቤተክርስቲያኒቱ ውጫዊ ተግዳሮቶች መነሻ መሰረታዊ ባህሪዎች የመለየት ችግር የለም።አነኝህ ሥራዎች ላለፉት ዓመታት በጥራት ግንዛቤ የወሰደ ከ70 ሚልዮን በላይ ምዕመን አለ።አሁን ያሉት ችግሮች የሚነሱት ከቤተክህነት አና ከመንግስታዊ የፖለቲካ አካላት መሆናቸው የችግሩ ስብጥር እና ጥግ በራሱ የተሰበሰበ መሆኑ ለመፍትሄዎቹ ግልፅ ያደርጋቸዋል። ይህንን ሁሉ በፍጥነት ለመመከት ግን ቤተክርስቲያኒቱ ውስጣዊ መዋቅሯን በፈጠነ መልክ ማዘመን መቻል ይጠይቃል።ይህንን ደግሞ ቁርጠኘነቱ እና በጎ ፈቃዱ ከቤተክህነት በኩል ካለ የቤተክርስቲያኒቱ ልጆች ለሥራው ዝግጁ ናቸው።


የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን በተመለከተ በጉዳያችን ላይ የወጡት ጽሑፎች መለስ ብሎ ለማየት ለሚፈልግ ከብዙ ጥቂቶቹን ብቻ ከአዚህ በታች ርዕሶቹን አና የተፃፉበትን ጊዜ (እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር)  ከስር ለማካፈል ሞክርያለሁ። ዛሬም ትኩረት የሚያስፈልገው ውስጣዊ የመዋቅር ማዘመን አንጂ በክርስቶስ ዘመን የነበረው አና  ክርስቶስ ተመልሶ አስከሚመጣ የሚኖረው  የውጭ ፈተና አይደለም። ይህ ማለት ውጫዊ ፈተናዎች በሙሉ ችላ ይባሉ ማለት አይደለም።የአንድ ተቋም ህልውና ግን አደጋ ላይ የሚወድቀው በውጫዊ ተፅዕኖ ሳይሆን ከውስጣዊ የአሰራር፣የመዋቅር አና የአቅም ግንባታ አለመጠናከር ነው።ቤተክርስቲያኒቱ  የውስጡን ስታጠናክር በፍጥነት የውጭውን ፈተና መመከት ብቻ አይደለም በጎ ተፅዕኖ የመፍጠር አቅሟን የሚጨምር ፈጣን አቅም ከመቅፅበት በራሱ ይመጣል።


ከአዚህ በፊት  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንን ፈተናዎች በተመለከተ ጉዳያችን ላይ ከወጡት ውስጥ የሚከተሉትን ለናሙናነት አቀርባለሁ።ማንም ሰው ጉግል ላይ ርዕሶቹን በመፃፍ ብቻ አያንዳንዱን ጽሑፍ በቀላሉ ማንበብ ይችላል።

የጉዳያችን የዛሬ መልዕክትም አንድ ነው። የኢትዮጵይ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንን  በቀላሉ ገፍቶ ኢትዮጵያን ማስቀጠል ፈፅሞ አይቻልም። የአርሷን ያህል የትህትናም ሆነ የፀጋ ባለቤት አሁንም የለም።ይህ ማለት የሌለውን የራሴ የሚለው የማመን መብቱን መጋፋት ወይንም ዝቅ አድርጎ ማቅረብ ማለት አይደለም።አውነታውን ማንም የማይነቀንቀው ሀቅ ነው።


ከእዚህ ቀደም በጉዳያችን ላይ የኢትዮጵያን ቤተክርስቲያን በተመለከተ ከወጡት ጽሑፎች ውስጥ የጥቂቶቹ ርዕሶች እና ሊንኮች : =


ርዕስ = የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አስተዳደራዊ ችግር በማያዳግም መልኩ ለመፍታትት ሁሉም ይነሳ! (ሚያዝያ፣2019 ዓም እኤአ)


ርዕስ = በኢትዮጵያ ኦ/ተ/ቤ/ክርስቲያን ላይ ሰሞኑን የነበረው ሁኔታ ለቤተክርስቲያን የደወል ድምጽ ነው::ወደፊት ምን ይሰራ? (መስከረም 6፣2019 እኤአ)

ርዕስ = የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አማኞችን ሁሉን አቃፊ የሆነ ፖለቲካዊ ዕሳቤ መሰረት ያደረገ የፖለቲካ ፓርቲ በመመስረት እና ሚናውን በማስፋት የኢትዮጵያ ህልውናን በትክክል ማረጋገጥ ይቻላል። (ጉዳያችን ሃሳብ) መስከረም 16፣2019 እኤአ የተፃፈ።


ርዕስ = የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ደህንነቷን ለመጠበቅ በፍጥነት መውሰድ የሚገባት ሁለት የመፍትሄ ርምጃዎች (የጉዳያችን ሀሳብ) (ህዳር 16፣2010 እኤአ የተፃፈ) 


ርዕስ = በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋኅዶ ቤተ ክርስቲያን ጉዳይ ላይ የሚታየው የመንግስት አያያዝ በኢትዮጵያ በአጭር ጊዜ ጦርነት ሊያስነሳ ይችላል (ጉዳያችን ልዩ እና ወቅታዊ ) (መስከረም 2019 ዓም እኤአ የተፃፈ)


ርዕስ = በጅማ ዩንቨርስቲ የ ኦርቶዶክስ ተማሪዎች ላይ ከ ሰሞኑ የተፈፀመ ግፍ (GUDAYACHN EXCLUSIVE ) (ጥር 2013 እኤአ የተፃፈ)


===============////=========

No comments: