አሁን ባለው የኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ትልቁ አጀንዳ በአማራ ክልል በታጣቂዎች እና በመከላከያ መሃከል እየተደረገ ያለው ጦርነት ነው።''ሁለት ሰዎች ሲጣሉ ችግሩ ቀላል ሊሆን ይችላል።ሁለት ሺህ ህዝብ ከሁለት ሺህ ህዝብ ጋር ሲጣላ ግን ጉዳዩ ጦርነት ነው '' የሚል አባባል አለ። በኢትዮጵያ አሁን እየሆነ ያለው ከተራ ግጭት ባለፈ ትርጉም የማይሰጥ የወንድማማቾች አሳዛኝ ጦርነት እየተደረገ ነው። ጦርነቱ ከመከላከያም ከታጣቂዎችም ሆነ ከሰላማዊው ህዝብ የሚወድቀው ኢትዮጵያ በአጭር ጊዜ የማትተካው ውድ የሰው ህይወት ነው። በአማራ ክልል አሁን ያለው ጦርነት መነሻ ምክንያት እና መፍትሄው በተመለከተ ከስድስት ወር በፊት ጉዳያችን ላይ ''የኦነግ/ኦህዴድ እና የህወሓት ጽንፈኝነት የአማራ ጽንፈኝነትን ወለደ። ኢትዮጵያን መልሰን ወደ አንደኛ ክ/ዘመን እንዳንከታት መንግስት የኃይል መንገድን ብቻ ከማሰብ ይልቅ ቀድሞ መከወን ያለበት ተግባር ላይ ያተኩር።'' በሚል ርዕስ ላይ ለመግለጽ ስለሞከርኩ እርሱን እዚህ ላይ ለመድገም አልፈልግም።ከእዚህ ይልቅ በወቅታዊው የአማራ ክልል ሁኔታ አንጻር ህዝቡ ያለበትን ነባራዊ ሁኔታ ዙርያ የተወሰኑ ነጥቦችን ላንሳ። እዚህ ላይ በአማራ ክልል ህዝብ ላይ በእዚህ ጦርነት ሳብያ እየደረሰ ያለውን ፈተና በውጭ የሚገኙ ዩቱበሮች ፈጽመው አያነሱትም።ዩቱበሮቹ ''ታጣቂዎች ይህንን ያዙ'' የሚል ዜና ላይ እንጂ በእዚህ ጦርነት የክልሉ ህዝብ የደረሰበት ማኅበራዊ፣ምጣኒያዊ ሐብታዊና ስነልቦናዊ ችግር ጥልቀት የሚናገር የለም።
ጉዳያችን - በጉዳያችን ሚድያ፣ኮምኒኬሽን እና ምክር አገልግሎት የሚዘጋጅ ሲሆን ከ2003 ዓም ጀምሮ በድረ-ገፅ ላይ የነበረ በአሁኑ ጊዜ ከአንድ ሚልዮን በላይ ጎብኚዎች ያሉት ገፅ ነው። Gudayachn is prepared by Gudayachn Multimedia, Communication and Consultant Organization. It has been online since 2011. Currently, Gudayachn is being visited by over One-million readers from all over the world.
ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages
Tuesday, December 5, 2023
በአማራ ክልል በሚደረገው ጦርነት ሳብያ የአማራ ክልል ህዝብ ላይ እየደረሰ ስላለው ሰቆቃ ያልሰማነው ከሰማነው ይበልጣል።
አሁን ባለው የኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ትልቁ አጀንዳ በአማራ ክልል በታጣቂዎች እና በመከላከያ መሃከል እየተደረገ ያለው ጦርነት ነው።''ሁለት ሰዎች ሲጣሉ ችግሩ ቀላል ሊሆን ይችላል።ሁለት ሺህ ህዝብ ከሁለት ሺህ ህዝብ ጋር ሲጣላ ግን ጉዳዩ ጦርነት ነው '' የሚል አባባል አለ። በኢትዮጵያ አሁን እየሆነ ያለው ከተራ ግጭት ባለፈ ትርጉም የማይሰጥ የወንድማማቾች አሳዛኝ ጦርነት እየተደረገ ነው። ጦርነቱ ከመከላከያም ከታጣቂዎችም ሆነ ከሰላማዊው ህዝብ የሚወድቀው ኢትዮጵያ በአጭር ጊዜ የማትተካው ውድ የሰው ህይወት ነው። በአማራ ክልል አሁን ያለው ጦርነት መነሻ ምክንያት እና መፍትሄው በተመለከተ ከስድስት ወር በፊት ጉዳያችን ላይ ''የኦነግ/ኦህዴድ እና የህወሓት ጽንፈኝነት የአማራ ጽንፈኝነትን ወለደ። ኢትዮጵያን መልሰን ወደ አንደኛ ክ/ዘመን እንዳንከታት መንግስት የኃይል መንገድን ብቻ ከማሰብ ይልቅ ቀድሞ መከወን ያለበት ተግባር ላይ ያተኩር።'' በሚል ርዕስ ላይ ለመግለጽ ስለሞከርኩ እርሱን እዚህ ላይ ለመድገም አልፈልግም።ከእዚህ ይልቅ በወቅታዊው የአማራ ክልል ሁኔታ አንጻር ህዝቡ ያለበትን ነባራዊ ሁኔታ ዙርያ የተወሰኑ ነጥቦችን ላንሳ። እዚህ ላይ በአማራ ክልል ህዝብ ላይ በእዚህ ጦርነት ሳብያ እየደረሰ ያለውን ፈተና በውጭ የሚገኙ ዩቱበሮች ፈጽመው አያነሱትም።ዩቱበሮቹ ''ታጣቂዎች ይህንን ያዙ'' የሚል ዜና ላይ እንጂ በእዚህ ጦርነት የክልሉ ህዝብ የደረሰበት ማኅበራዊ፣ምጣኒያዊ ሐብታዊና ስነልቦናዊ ችግር ጥልቀት የሚናገር የለም።
Sunday, November 26, 2023
በውግዘት ውስጥ ላሉት፣አሁንም በድፍረት ለሚሄዱት ለትግራይ የቀድሞ ጳጳሳት አልቅሱላቸው።
- አክሱም ጽዮን በክርስትና ታሪክ ለሁለት ሺህ ዓመታት ያህል ያላየችውን የድፍረት ስራ በቅዱስ ሲኖዶስ በተወገዙት የትግራይ አባቶች እያየች ነው።
- የእነርሱን አካሄድ እየተመለከተ ዝም ብሎ የሚገለገለው የትግራይ ምዕመን፣ የእዚህ ዓይነት አካሄድ ከአባቶቻችን አልተማርንም ተዉ! ማለት ይገባዋል።
አሁን የትግራይ አባቶች ከቀልባቸው አይደሉም።ምን እያደረጉ እንደሆነ፣ምን እየሰሩ እንደሆነ ከአዕምሯቸው ጋር ስላልሆኑ አያውቁትም። አሁን የሚያስፈልጋቸው የሚያደርጉትን አያውቁምና የሚያለቅስላቸው፣ ወደ ቀልባቸው መልሳቸው ብሎ የሚያነባላቸው ሰው ያስፈልጋቸዋል። የእነርሱን አካሄድ እየተመለከተ ዝም ብሎ የሚመለከተው የትግራይ ምዕመንስ? ቢያንስ የእዚህ ዓይነት አካሄድ ከአባቶቻችን አልተማርንም አይልም? በመንደር ተሰባስቦ ከቅዱስ ሲኖዶስ አንድነት ወጥቶ እንደፈለጉ በመሄድ የሚሰጥ ስልጣነ ክህነትን የትግራይ ምዕመናን ከአባቶቻችን አልተማርነውም።ከየት አመጣችሁት ብሎ አይጠይቅም?
እናታችን ጽዮን በማኅበረ ቅዱሳን የመዝሙር ልዑክ
Saturday, November 25, 2023
የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን ''ስታትስቲክስን'' መሰረት ያደረጉ ዝግጅቶቹ ከአዲሱ ትውልድ ዘመናዊ አቀራረብ ጋር የቴሌቭዥንን ስም እያላቀው ነው።ማየት ማመን ነው።ለናሙን ይህንን ዝግጅት እና አቀራረብ ይመልከቱ (ቪድዮ)
ኢትዮጵያ ያለመችው ኃያላኑ የሰፈሩበት ባህር
Tuesday, November 21, 2023
አቡነ ኤርምያስ ከተናገሩት ውስጥ እውነት ያልሆነ አንድ ቃል ማግኘት አልቻልኩም።
- ''በማንም ተጽዕኖ ውስጥ ወድቄ በማንም ተናገር ተብዬ የተናገርኩት የለም.።ወደፊትም እናገራለሁ ብዬ አላስብም።መንፈስቅዱስ ይጠብቀኝ። '' አቡነ ኤርምያስ የሰሜን ወሎ ሀገረስብከት ሊቀ ጳጳስ
=========
ጉዳያችን ምጥን
ቤተክርስቲያንን ከፖለቲካ ዕይታቸው አንጻር ለመለወስ እና ጥፋት ነቁጥ ለመንቀስ የሚደክሙ በየትኛውም የጎሳ ስብስብ ውስጥ ቢሆኑ ከላይ ከተጠቀሱት ከፈሪሳውያንና ከሔሮድስ ወገን አስተሳሰብ የተለዩ አይደሉም። አቡነ ኤርምያስ የአባትነታቸውን የተናገሩትን እውነት ለአንዳንዶች የራስ ምታት ቢሆንባቸውም ዕውነትነቱ ላይ ግን የሚያመጣው አንዳች ለውጥ የለም።
''አራት ኪሎ ቢገባስ''
''ላሊበላ ለምን ከተሙ?''
''በጦርነት ሰላም አይመጣም፣ ወንድም ወንድሙን አጥቅቶ፣ፋኖ መከላከያን አጥቅቶ ወሰን ሊያስከብር አይደለም፣ ጉዳዩ ይህ እንደ ሀገር ያሰጋል።''
- የተቆጡ ወገኖች አሉ።ሁላችንም እኔንም ጨምሮ ተቆጥተናል።
- እነኝህ ወገኖች ከመከላከያ ጋር አብረው የተዋደቁ ናቸው።
- መንግስት ዝቅ ብሎ ለእነኝህ ወገኖች የሚመጥን መድረክ መንግስት አዘጋጅቶ መፍትሄ ማምጣት አለበት።
- ክርስቶስ ዝቅ ብሎ መጥቶ አዳምን አድኖ የነበረበትን መንገድ ምሳሌ ጠቅሰዋል።
- መከላከያ ከገባ በኋላ ተፈጽሟል የተባለውን ዘረፋ መከላከያ አጣርቶ ይህንን ያደረጉትን እንዲቀጣ አሳስበዋል።
- ''የመረረው ድሃ ይገባል ከውሃ'' እንዲሉ መንግስት ባለበት ሀገር ዛሬ ከዋና ከተማዋ ተነስቶ ሰው እንዴት ለመሄድ የሚፈራበት ሁኔታ ይፈጸማል?
Tuesday, November 14, 2023
በአጼ ቴዎድሮስ፣ቀዳማዊ አጼ ኃይለሥላሴና ኮ/ል መንግስቱ ላይ የሰራነውን የመሪዎቻችንን በጎ ሀሳብ የመጎተት ክፉ ባሕል በጠ/ሚ/ር ዐቢይ ላይ አንደግምም!
- ዛሬ አጼ ቴዎድሮስ፣ቀዳማዊ አጼ ኃይለስላሴ፣ ኮ/ል መንግስቱ እያልን ስንጣራ መሪዎቹን ክነበረ ህልማቸው በየዘመናቸው ያልጎተትን ጨዋዎች እንመስላለን።
============
ለመጠቅለል፣ በአጼ ቴዎድሮስ፣ቀዳማዊ አጼ ኃይለሥላሴና ኮ/ል መንግስቱ ላይ የሰራነውን የመሪዎቻችንን በጎ ሀሳብ የመጎተት ክፉ ባሕል በጠ/ሚ/ር ዐቢይ ላይ አንደግምም። ኢትዮጵያ እንደቀደሙት ዘመናት አትታለልም። ትውልዱም ካለፈው ስህተት በብዙተምሯል።ከዘመን እና ትውልድ አሻጋሪ የመሪዎች ሀሳብን በማንም የባዕዳን እና የባዕዳን ቁራሽ ተመጽዋች እግር ጎታች ሀሳብ አንቀይረውም።
Monday, November 6, 2023
የአማራ ክልል ህዝብ የወደቀበትን የመከራ መአት የሚያወራለት አንድም ''ዩቱበር'' አጥቷል። ህዝብ የገባበት ማጥ ሌላ፣ በውጭ ሃገር ሆነው የጥይት ባሩድ የማይሸታቸው የሚያወሩት ሌላ ሆኗል።ስለ የህዝቡ መከራ የሚናገር የለም።ዩቱበሮች ጦርነት ህዝብ የማይጎዳበት አበባ የመበተን ያህል አስመስለው ሲናገሩት ''አጀብ'' ያሰኛል።
- ''ከ3 ሚልዮን በላይ ተማሪዎች እስካሁን ትምሕርት ለመጀመር አልተመዘገቡም'' አቶ መኳንንት አደም የክልሉ ምክትል ትምሕርት ኃላፊ፣
- ከፍተኛ ረሃብ በክልሉ በተለይ በጃናሞራ መግባቱ ተሰምቷል።የምክር ቤቱ አባል በአቶ ባያብል ሙላቴ የተራቡትን ለመደገፍ እንቅስቃሴ ተጀምሯል።
- ክልሉ ከአሁኑ ጦርነት በፍጥነት መውጣት ካልቻለ በተጨማሪ የወራት ጦርነት በልማት 60 ዓመታት ወደኋላ ሊቀር ይችላል።
- ዝምታው ይሰበር።
ከእዚህ ሁሉ በተለየ በጃናሞር ያለውን የድርቅ ጉዳት ለመደገፍ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጃናሞራ ተወካይ አቶ ባያብል ሙላቴ እያስተባበሩ የሚገኙት የቴሌግራም ግሩፕ ላይ በጎ አድራጊዎች የቻሉትን እያደረጉ ይገኛል። የገንዘብ ማሰባሰብያ የባንክ ሂሳብ በጥምረት ማለትም በአቶ ባያብል ሙላቴ፣ፕሮፌሰር ጌታሁን መንግስቱ እና በወ/ሮ እኝሽ ገብሬ እንዲንቀሳቀስ የተደረገ ሲሆን በቴሌግራሙ ገጽ ላይ የተለጠፈው የሂሳብ ቁጥርም ከስር እንደሚከተለው ይታያል።
================================================================
Friday, November 3, 2023
Ethiopia’s prime minister wants a Red Sea harbour
Ethiopia’s neighbours are rattled, particularly because Abiy had not raised the issue with them before making his threats. “The whole country thinks the man is mad,” says an adviser to Somalia’s president. A fight over ports would further destabilise a region already in turmoil. Sudan, Ethiopia’s neighbour to the west, has been plunged into what the un calls “one of the worst humanitarian crises in recent history”. Fighting between two warlords there has forced almost 7m people from their homes. And Ethiopia itself faces simmering rebellions in Oromia, its largest and most populous region, and Amhara.
Abiy says that Ethiopia’s demands can be met through peaceful negotiations with its neighbours. Better to discuss the matter now, he argues, than to risk an armed conflict in the future. But Abiy has reportedly said in private that he is ready to use force if talks fail. “If it is not achieved by other means, war is the way,” says an Ethiopian official. A few days after the broadcast Abiy flexed his muscles with a military parade in the capital, Addis Ababa, in which the army displayed its new weapons including a Russian-made electronic-warfare system. Troop movements have been detected along both sides of Ethiopia’s border with Eritrea in recent weeks. A well-connected source in Addis Ababa says that the armed forces are exercising in preparation for another conflict. On October 22nd the head of the air force warned his troops to ready themselves for war.
Ethiopia’s Red Sea conundrum dates back to at least the start of its bloody border war with Eritrea in 1998. Though a ceasefire was reached in 2000, the two countries remained at loggerheads. Ethiopia could not ship goods through Assab and Massawa. Now 90-95% of its external trade flows through Djibouti, to which it pays some $1.5bn a year in port fees.
In 2018, soon after Abiy came to power, he ended the nearly two decades-long stand-off with Eritrea by signing a peace deal with its dictator, Issaias Afwerki. Though the contents of the deal were never made public, it was generally understood that Ethiopia would regain tax-free access to Eritrea’s ports in exchange for returning disputed territories it had occupied since the end of the war. The following year Abiy was awarded the Nobel peace prize.
But plans for Ethiopia to use Eritrea’s ports never materialised. Instead, two years later, a power struggle between Abiy and Tigray’s ruling party, the Tigrayan People’s Liberation Front (tplf), sparked civil war. Eritrean troops joined in on Abiy’s side to fight against the tplf, which Issaias has long hated.
The two leaders have fallen out since then, possibly because Ethiopia signed a peace deal with the tplf in late 2022. Each sees the other as a threat to their influence over the region. “Abiy and Issaias cannot co-exist in this region,” says an Ethiopian opposition leader. “War is inevitable.”
Increased tensions with Eritrea could exacerbate Ethiopia’s existing internal conflicts. Under the peace deal Abiy struck with the tplf last year, it was supposed to disarm and demobilise its fighters while Eritrea was meant to withdraw its forces from Tigray. But Eritrea remains in control of at least 52 districts of northern Tigray, according to the region’s interim administrators. In recent weeks, Eritrean troops have expanded their presence along the border areas, reports a visiting foreign researcher. Tigrayan forces have handed over most of their heavy weaponry to the Ethiopian army. But they still have some 200,000 men and women under arms.
Another party in the multi-sided civil war in Tigray was Ethiopia’s Amhara regional government, which sent its own militias and troops to fight alongside Abiy’s federal forces. These troops were also supposed to have withdrawn from disputed territories inside Tigray that they occupied at the start of the war. But they have yet to do so. Instead, they have turned on Abiy’s government, accusing it of betraying Amhara’s interests. In August they fought federal forces for control of several towns.
Shifting alliances
With so much bad blood and so many armed groups jostling for influence within Ethiopia, Abiy’s threats are extremely reckless when it comes to his own country’s security. They are damaging to Ethiopia’s relations in the wider region. Djibouti, which now provides Ethiopia’s main access to the sea, has furiously responded that its “territorial integrity cannot be disputed”. Somalia, similarly, insisted its territorial integrity and sovereignty are “sacrosanct and not open for discussion”.
Some Ethiopian officials play down Abiy’s fighting talk. “It’s about diverting attention from domestic issues,” says an ally of the prime minister. Although the Eritrean port of Assab, which was once part of the former Ethiopian Empire, has particular symbolic value for Ethiopians, Abiy has also floated the possibility of negotiating for a strip of land around the ancient port of Zeila in the breakaway Somali region of Somaliland. In exchange, Ethiopia might offer to recognise Somaliland statehood. “Abiy has no interest in being part of another conflict for the moment,” says an analyst in Addis Ababa.
But the Ethiopian prime minister is notoriously unpredictable. “Nobody except himself can be certain if he is serious or not,” says a tplf official. Little more than three years ago Abiy insisted he would not go to war in Tigray. Many diplomats and regional leaders took him at his word, which he soon broke. They would be wise not to make the same mistake again.
==================////===========
Thursday, October 19, 2023
ኢትዮጵያ ባነሳችው የባሕር በር ጉዳይ ላይ አንድም የአውሮፓ፣የሰሜን አሜሪካ፣ደቡብ አሜሪካ፣እስያና አውስትራልያ ሀገር ትክክል አይደለም ያለ መንግስት የለም።
- የአፍሪካ ሕብረትም ሆነ የተባበሩት መንግስታት በጉዳዩ ላይ ምንም አለማለት፣ሁለቱም በኢትዮጵያ የወደብ ባለቤትነት ጉዳይ ላይ ቅንጣት ታክል ጥርጣሬ እንደሌላቸው በትክክል ያሳያል።
ጉዳያችን
============
የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል ቀን ክብረ በዓል እንደ ኢትዮጵያ አቆጣጠር 1979 ዓም ጥር ወር በቀይባሕር ላይ ሲያከብርና ዕጩዎችን ሲያስመርቅ
Friday, October 13, 2023
ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ለኢትዮጵያ የባሕር በር አስፈላጊነት የህልውና ጉዳይ መሆኑን ገለጹ።ለኢትዮጵያ ሕዝብ ተወካዮች ምክርቤት ያደረጉት ገለጻ ሙሉ ቪድዮ - '' Seaport issue to Ethiopia is a question of existence'' PM Abiy Ahmed speaks to Ethiopian MPs.
Thursday, October 12, 2023
የቀይ ባሕርን እውነት ጠ/ሚ/ር ዐቢይ ሲናገሩት ስህተት፣ሌላው ሲያወራው እውነት ሊሆን አይችልም። እራሳቸው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ የማይክዱትን እውነት ለማስተባበል አንሞክር።
- ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ስለ ቀይባሕር አሁን የተናገሩት ''አቅጣጫ ለማስቀየር'' ነው የሚለው አሉባልታ ውሸት ለመሆኑ ግልጽ የሆኑ ማስረጃዎች አሉ።
- በዓለም ላይ የሚደረገው ንግድ አውሮፓን ከመካከለኛው ምስራቅና ከሩቅ ምስራቅ ጋር የሚያገናኘው የቀይ ባሕር በተባበሩት መንግስታት ግምት መሰረት በዙርያው አሁን ካለው ህዝብ ብዛት እኤአ 2050 ዓም 343 ሚልዮን የሚደርሰው ይህ አካባቢ አንድ ሺህ ኪሚትር እርዝመት ያለው የባሕሩ ክፍል አስር ሚልዮን የማይሞላ ህዝብ ባላት ኤርትራ ብቻ ሰላሙ ይጠበቃል ብለው ስለማያምኑ፣
- ቀይባሕርን ለመቆጣጠር አንዳንድ የመካከለኛ ምስራቅ ሀገራት የያዙት አጀንዳ በምስራቁም በምዕራቡም ሀገራት በተለያየ የስጋት ደረጃ ላይ መውደቁ፣
- አሜሪካ፣ሩስያ ወይንም ቻይና በቀጥታ የቀይባሕርን በብቸኝነት መቆጣጠር ስለማይችሉ እና አንዳቸው አንዳቸውን ስለሚጠባበቁ ከእዚህ ሁሉ እንደኢትዮጵያ በህዝብ ብዛት ከ120 ሚልዮን ህዝብ ባላት ኢትዮጵያ ቢጠበቅ ያላቸው ፍላጎት መኖሩ፣
- አቶ ኢሳያስ የዕድሜያቸው መግፋት ተከትሎ በቀጣይ ኤርትራን የሚመራ ጠንካራ አመራር በሌለበት ሁኔታ አቶ ኢሳያስ በድንገት ቢያልፉ በኤርትራ በሚነሳው የስልጣን ሹክቻ ሀገሪቱ ወደየከፋ የእርስ በርስ ጦርነት ከገባች የቀይ ባሕር ባልተጠበቀ መልኩ በሽብርተኞች እጅ እንዳይወድቅ የሁሉም ኃያላን መንግስታት ስጋት ብቻ ሳይሆን የእስራኤልም ቀዳሚ ስጋት መሆኑ፣
- የመጨረሻው ምክንያት እጅግ ወቅታዊው የፍልስጤም እስራኤል ጦርነት መልሶ ማገርሸቱ፣አሜሪካ ጦሯን ወደ መካከለኛው ምስራቅ በብዛት መላክ መቀጠሏን አስታኮ የመካከለኛው ምስራቅ ግጭት ከፈነዳ አንዱ ትኩረት የሚሆነው መንግስት አልባዋ የመንን የመፋለምያ ሜዳ አድርጎ ቀይባሕርን የማወከ ተግባሩ ስለሚባባስ ይህንን አሁንም ኤርትራ ለመቆጣጠር በሰው ኃይልም ሆነ በሃብት ፍሰት መቋቋም ስለማትችል አሁንም ለተለያዩ ኃይሎች ጋር በተለይ ጸረ ምዕራብ ከሆኑት ጋር የመዋዋል አደጋው አፍጥጦ በመምጣቱ፣
Sunday, October 8, 2023
በቋፍ ላይ የነበረው የዓለማችን አጠቃላይ ፀጥታ አደጋ ላይ ወድቋል፣የተፈራው የፍልስጤም-እስራኤል ጦርነት ተቀስቅሷል፣ሀገራት ጎራ መለየት ጀምረዋል።
- የአሁኑ የፍልስጤም እስራኤልን ጦርነት ለዓለማችን የከፋ ከሚያደርጉት ውስጥ ስድስቱ ምክንያቶች
የአሁኑ የፍልስጤም እስራኤልን ጦርነት ለዓለማችን የከፋ ከሚያደርጉት ውስጥ ስድስቱ ምክንያቶች :
- የሩስያ ዩክሬን ጦርነትን ተከትሎ በምዕራቡና ሩስያ፣ቻይና መሃል ያለው ውጥረት ከመቼውም ጊዜ በከፋ ሁኔታ ላይ መሆኑ፣
- የተባበሩት መንግስታት በተዳከመበት እና የዓለምን ጸጥታ ችግር የመፍታት አቅሙ በተደጋጋሚ ተፈትኖ በወደቀበት ጊዜ መሆኑ፣
- የጸጥታው ምክር ቤት አምስቱ አባላት በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ የጋራ አጀንዳቸው በሳሳበት እና ለእዚህም አንድ ዓይነት መፍትሄ ገና ባላገኙበት ወቅት መሆኑ፣
- የሰሜን አትላንቲክ ቃልኪዳን ሀገሮች ውስጥ አባል የሆነችው ቱርክ በፍልስጤም እስራኤል ጉዳይ የምትወስደው አቋም ለድርጅቱ የራሱ የሆነ ጥላ ማጥላቱ፣
- ከኮቪድ በኋላ የተጎዳው የብዙ ሀገሮች ምጣኔ ሀብት በፈጠረው የኑሮ ውድነት ሳብያ በብዙ ሀገሮች ያለው የውስጥ ቅራኔ በተባባሰበት ጊዜ መሆኑና ይህም በብዙ ቦታዎች ''ግልገል ጦርነቶች'' የመፍጠር አደጋ መኖሩና
- የምዕራቡን ዓለም በማስተባበር የመሪነቱ ሚና የነበራት አሜሪካ በአሁኑ ጊዜ ያላት ፕሬዝዳንት የነቃና የተጋ አለመሆን ብቻ ሳይሆን ሰላማዊ መፍትሄ የማምጣት አቅሙ ያነሰ መሆኑ የሚሉት ይጠቀሳሉ።
Thursday, September 21, 2023
''አክቲቪዝም ከጆርናሊዝም'' የደባለቀባቸው ዩቱበሮች በአማራ ክልል የሚፈሰው የመከላከያ እና የአማራ ክልል ህዝብ ደም አልታያቸው ብሏል። በኢትዮጵያ ህዝብ አንድ ሊባሉ ይገባል።
- የሰው ደም እየፈሰሰ መከላከያና የአማራ ክልል ታጣቂ ኃይል አይነጋገር የሚሉት በውጪ ሀገር ሶፋ ላይ የተቀመጡት መሆናቸውን ልብ ይሏል።
- የሰላም ንግግሮችን ለማጣጣል የሚሞክሩትን አጥብቀን መቃወም ኢትዮጵያዊ የውዴታ ግዴታችን ነው።
ባጠቃላይ የባዕዳን ጣልቃ ያልገባበት የመነጋገር እና ኢትዮጵያ ከገባችበት የፖለቲካ ቅርቃር የሚያውጣ የመፍትሄ መንገድ ከመንግስትም ከፋኖም ይጠበቃል። አሜሪካን አውሮፓ ቁጭ ብለው መንግስት ለመገልበጥ ነው መሄድ ያለብህ የሚለው ስብከት ኢትዮጵያን ወደ መበተን ደረጃ የሚያደርስ አደገኛ አካሄድ ስለሆነ ጆሮ ሊሰጠው የሚገባ አይደለም። መንግስት ይቀየራል።የሚቀየረው ግን በጦርነት ክልልን በማውደም አይደለም። ትግል ሲያስፈልግ በመቶዎች የሚቆጠሩ የሰላማዊ ትግሎች መንገዶች አሉ።ከእዚህ ባለፈ የምርጫ ሰሌዳን ተከትሎ ህዝብ በነቂስ ወጥቶ የሚፈልገውን በመምረጥና ድምጹ እንዲከበር በመታገል ወደ የሚፈለገው ለውጥ መምጣት ይቻላል።ቢያንስ በ21ኛው ክ/ዘመን መንግስት ባልሰለጠነ መንገድ በማውረድ ሀገር ከመበተን መታደግ የሁሉም ግዴታ መሆኑን ማወቅ አለብን።ከእዚህ ጋር የሰላም ንግግሮችን ለማጣጣል የሚሞክሩትን አጥብቀን መቃወም ኢትዮጵያዊ የውዴታ ግዴታችን ነው።
Saturday, September 16, 2023
Is the biblical ark of the covenant hidden in an Ethiopian church?
ሙሉውን ጽሑፍ ከስር ያንብቡ።
Is the biblical ark of the covenant hidden in an Ethiopian church?
- Researchers claim the ark hidden for 3,000 years in Ethiopia.
Sunday, September 3, 2023
የግሪካውያን የኢትዮጵያ ወዳጆች ማኅበር እና በኢትዮጵያ የግሪክ ማኅበረሰብ አመራሮች በጣልያን፣ፈረንሳይና ግሪክ የኢትዮጵያ ክብርት አምባሳደር ዴሚቱ ሃሚሳ ጋር በአቴንስ ከተማ ተገናኙ። የግሪካውያን የኢትዮጵያ ወዳጆች ማኅበር እኤአ መስከረም 30/2023 አቴንስ ላይ ልዩ ዝጅግት አዘጋጅቷል።
- ''በአዲስ አበባ የሚገኘው የግሪክ ኮሚኒቲ ከመንግስት ጋር የገባውን ችግር በተመለከተ ጉዳዩ በፖለቲካና ዲፕሎማሲያዎ ደረጃ የሚፈታ ነው '' ክብርት አምባሳደር ዴሚቱ ሃሚሳ
በውይይቱ ላይ አምባሳደር ዴሚቱ በሰጡት ምላሽ :
MEETING OF THE ASSOCIATION OF GREEKS OF ETHIOPIA (A.G.E.) WITH THE ETHIOPIAN AMBASSADOR
On Thursday, August 24th, at the MELIA Hotel in Athens, a delegation of the Board of Directors of A.G.E., consisting of the 2nd Vice President Mr. Georgios Michaelides, the Treasurer Mr. Theodoros Panas and the member of the Board of Directors Mr. Dimitrios Stragalis, together with the President of the Greek Community Association of Addis Ababa Mr. Odysseas Parris, had a meeting with the Ambassador of Ethiopia to Italy who is accredited in Greece Mrs. Demitu Hambisa Bonsa, who was accompanied by the Second Secretary of the Embassy Mr. Addisu Melkamu Kebede.
The 2nd Vice President, referred to the intervention of the A.G.E. to the Municipality of Athens when rumors circulated about renaming of the historic Abyssinia Square in Monastiraki and the assurance of the Mayor of Athens Mr. Kostas Bakoyannis that there is no such intention. The Mayor supported the proposal of A.G.E. for the placement of a memorial monument and signage.
The 2nd Vice President noted the positive response of the Ethiopian Community living in Greece to the initiative to create this monument that will mark the long-standing relations between the two peoples. He said that the cost will be covered by sponsorships and actions of members and friends of S.E.A and Ethiopian Communities living in Greece and other countries abroad. He stressed that if the amount raised exceeds the cost of the monument, the remaining amount will be allocated to the BORENA area for the creation of a drinking water well, according to the wish of the Ethiopian Community in Greece.
The September 30, 2023 event at Abyssinia Square will mark the beginning of the celebrations for a century of the renaming of the Square by decision of the Municipality of Athens in 1924 to Abyssinia Square after the significant donation given by Ethiopia to the Greek refugees of the Asia Minor Catastrophe, and the over a century establishment of diplomatic relations.
The President of the Greek Community Association of Addis Ababa, reported on actions and claims of the Ethiopian Ministry of Education, which attempted to convert the English section of the Greek Community Schools owned by the Greek Community Association of AA, into a Charitable Endowment. A form that means the transfer of ownership of the school buildings through the Endowment to the Ethiopian State and dispossession of the Community's property. For the operation of the English section, the Greek Community Association of AA has established a new organization provided by the legislation for establishing an INTERNATIONAL SCHOOL from the 2023-24 school year and requested permission, which was not granted. He stressed that we are not a Community that wants to run to court but a Community that operates respecting Ethiopian laws.
He referred to the fact of the appointment of an Interim Administration by designs of the Ministry of Education, without any discussions or consultations, for the management of the English section of the school. The Interim Administration has exceeded its mandate by prohibiting the Board members of the Community to have access to the premises of the Community, issuing orders for the removal of residents from the houses that the community had provided them, etc. Still in excess of its authority, it is involved in purely community matters such as its social policy on indigent people, the management of the Greek St. Frumentius Church, the Cemetery, etc. Lastly they interfere in the Greek Section of the Schools that operate under the Greek Ministry of Education.
He pointed out that in May, the country's auditing mechanisms have taken the accounting documents of the Community for audit. No findings have been announced and the Bank accounts of both the Community and the personal accounts of the members of the Board of Directors of the Community have been frozen, despite the fact that the current Board, it is only one year in office, and since the beginning it met with this situation of interference.
He informed the Ambassador that the ownership of the Community Schools is not the same as the other schools where land was allocated for building. The Greek Community Schools were built on land which was purchased by the Greek community from the donations and sponsorships of its members.
The 2nd Vice President pointed that the Greek Community Association of AA has the full support of A.G.E., since A.G.E. represents the vast majority of the Community members living in Ethiopia at the time of the great exodus, who created and sustained the Community property, and that were forced to leave by the Derg Regime in 1975-76.
The Treasurer, Mr. Panas Theodoros, informed about the Marathon Road Museum and the request of the Municipality of Marathon to enrich the museum with exhibits from Ethiopian marathon runners. He also mentioned the cooperation of the A.G.E. with the "Pelargos" Association, which are families who have adopted children from Ethiopia, to teach Ethiopian culture to these children. From the bilingual books of "Pelargos” a part goes to support the literacy of young people in Ethiopia.
The Ambassador's statement was:
The long-standing relations between the two peoples have been strong and we must continue to deepen them. Relations that go back for hundreds of years.
The issue of the School will be resolved at the political and diplomatic level and she stressed that it is not the intention of the Ethiopian Government to take over the Community property. She regretted the turn the matter had taken.
On the issue of the monument in Abyssinia Square, she said that it is a very important initiative because that will show to future generations the relations between the two peoples. The initiative should be raised to a higher level, with the participation of the Ethiopian Ministry of Tourism and Culture, and when the unveiling ceremony is held, the two Prime Ministers should be invited to be present. She said that they have a wish that the monument should be jointly designed and reflect the long-standing relationship between the two peoples and asked to see the proposal of A.G.E.
She pointed out that they are planning some event for Abebe Bikila in Athens in October, of which they will inform A.G.E. in due time.
Regarding the marathon road museum, the Embassy's Second Secretary said that he would support the effort and took the initiative to find exhibits.
On the part of A.G.E. thanks were expressed for the time the Ambassador took to inform the Association and invited her on her next visit to be received at the A.G.E. offices for a briefing and then to have a dinner.
The whole discussion took place in an extremely friendly and family-like environment and all agreed to continue the constructive channel of communication that has started.
On August 25, a meeting took place between the President of A.G.E. Dr. Alexandros Grous, who came urgently and met with the Ambassador of Ethiopia.
የኤርትራ አምባገነናዊ አስተዳደር በመጨረሻ እያበቃለት ይሆን? ዕውቁ የፖለቲካ ፕሮፌሰር ጄምስ አዲስ ትንታኔ Is Eritrea’s Dictatorship Finally Ending? Prof James Ker-Lindsay - Latest Video
Prof James Ker-Lindsay Is Eritrea’s Dictatorship Finally Ending?

-
የቅዱስ ላልይበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ጉዳያችን/ Gudayachn ሰኔ 2/2011 ዓም (ሰኔ 8/2019 ዓም) ግንቦት 29/2011 ዓም ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል በለቀቀው ዜና እንዲህ ይነበባል: - ...
-
Gudayachn Report August 14,2020 Senior Hydrologists and water resource Engineers webinar presentation and discussions on creating awareness ...
-
በ ካርታ ጫወጣ ጎበዝ አደለሁም። ግን ጆከር የተባለች ካርታ መኖሯን አውቃለሁ።ጆከር ካርታ በ ሁሉም ቦታ ስለምትገባ በ ካርታ ጫወታ ጆከር የደረሰው ሰው የማሸነፍ እድል ስላለው ፊቱ በ ፈገግታ ይሞላል። የ አትዮጵ...