ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Thursday, March 7, 2019

የኢትዮጵያ ፖለቲካ አልተወሳሰበም የበለጠ እየጠራ ነው።ወሳኝ እርምጃ ከሕዝብ እና ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ይጠበቃል።


ጉዳያችን / Gudayachn 
የካቲት 29/2011 ዓም (ማርች 8/2019 ዓም)
  • ኦዴፓ ውስጥ ያለው ፅንፈኛ አካል ዶ/ር ዓብይን ከስልጣን  የማውረድ ሴራው ተደርሶበታል ፣
  • የፅንፍ ኃይሎች ካሰቡት ጊዜ በፊት ለምን ወደ ነውጥ እንዲገቡ ተገደዱ?
  • የጠቅላይ ሚኒስትሩ የመረረ እርምጃ የትግራይን የተመረጡ የመሳርያ ክምችት (ሰላማዊ ሕዝብን ባልነካ መልኩ) በአየር ኃይል ከመምታት እስከ ኦዴፓ ውስጥ ያሉ ፅንፈኞችን እና የጃዋር ግልፅ ህዝብን የማሸበር ተግባር  ለፍርድ እስከማቅረብ ድረስ መሄድ  ወሳኝ ሀገር አድን ስራዎች ናቸው።
=============================================
''ዶ/ር ዓብይ ጠቅላይ ሚኒስትር መሆን የለበትም''  ጃዋር  ከአመት  በፊት

ልክ የዛሬ ዓመት የኦሮምያ ሚድያ ኔትዎርክ ላይ ጀዋር መሐመድ ቀርቦ ''ዓቢይ ወደ ስልጣን ፈፅሞ መምጣት የለበትም።ከሆነ ለማ ወደ ጠቅላይ ሚኒስትርነት መምጣት አለበት '' አለ።ይህንን ሲናገር እንደተለመደው አየር እንዳጠረው ሕፃን እጆቹን እያወራጨ ነበር።በሚቀጥለው ቀን ቃለ መጠይቁም ዶ/ር ዓቢይ ፈፅሞ ወደ ጠቅላይ ሚኒስትርነት ቢመጣ "አንቀበልም" በማለት ተናገረ።የኢትዮጵያ ፓርላማ ግን   ዶ/ር ዓቢይን ጠቅላይ ሚኒስትር አድርጎ መረጠ።

በህዝባዊ አመፅ እና በኢህአዴግ -ህወሓት መሐል ከተፈጠረው ቅራኔ ሳብያ የቀድሞዎቹ ኦህደድ እና ብአዴን የህወሓትን አብዮታዊ ዲሞክራሲን አሽቀንጥረው ለውጥ እና የለውጥ ኃይል በሚል አዲስ እንቅስቃሴ ከተጀመረ እና ዶ/ር ዓብይ የመጋቢት 24/2010 ዓም ንግግራቸው እንደተሰማ በብዙዎች ዘንድ ከፍተኛ ተስፋ ሰጥቶት አንድ ዓመት ዘለቀ።በእነኝህ አስራ ሁለት ወራት ውስጥ ባጭሩ ለማስቀመጥ የነበረው የፖለቲካ ውጥረት መርገብ ችሏል።

ኦዴፓ ውስጥ ያለው ፅንፈኛ አካል ዶ/ር ዓብይን ከስልጣን ለማውረድ ሴራው ተደርሶበታል

ባለፉት አስራ ሁለት ወራት ውስጥ በኦዲፓ እና አዲፓ መሓከል እና እንደ ኢህአዴግ አጠቃላይ በለውጡ ውስጥ የነበረው የስልጣን ድልድል ጠርቶ ስላልታዬ ጉተታው በግልጥ መታየት በተለይ ላለፉት አራት ወራት በግልጥ እየታየ ነው።ይህ በእንዲህ እያለ ኦዴፓ ውስጥ የተነሳው የመደመር አስተሳሰብ አራማጅ ኃይልን ለመሸርሸር  የኦነግ እና የጃዋር አንጃዎች ቀድሞ ከነበራቸው የኦዴፓ ወኪሎቻቸው ጋር መዋቅር የማስፋት ሥራ ጀመሩ።በእዚህ የመዋቅር ማስፋት ሥራ ውስጥ ፅንፈኛው አካል እንደ አሜባ እራሱን እያሰፋ መጥቶ አቶ ለአቶ ለማ እና ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አጀዳ መስጠት ሲፈልግ ያለችው አንዲት የከረመች አጀንዳ የአዲስ አበባን ጉዳይ አገኝቶ እርሷኑ ማጮህ ጀመረ።አጀንዳው የተነሳበት ጉዳይ ፅንፈኛው ኦዴፓ ውስጥ ያሉ ለዘብተኞች የሚባሉትን እና የአንድነት ኃይል ጋር ይሰራሉ የሚባሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይን ጨምሮ  ከስልጣን ለማስወገድ እና ስልጣን ለመንጠቅ የሸረቡት ምንም ዓይነት ሴራ የለም ማለት አይደለም። በእዚህ ጉዳይ ደግሞ ከውጭ ጉዳይ ወርቅነህ ገበየሁ ጀምሮ አንዳንድ የኦዴፓ አባላት ዶ/ር ዓብይን ከስልጣን አውርዶ የፅንፈኛ አካል ወደ ስልጣን እንዲመጣ ለማድረግ የሚሞከሩ እንዳሉ ሲሰማ ከርሟል።

ፅንፈኛው አካል በመስቀል አደባባይ በጠቅላይ ሚኒስትሩ  ላይ የግድያ ሙከራ ሲደረግ ከህወሓት ጋር አልተባበረም ወይ? የሚለው ጥርጣሬ ወደፊት የሚገለጥ ይሆናል።በሰሞኑ የፅንፈኛው ኦዲፓ  ለስልጣን ነጠቃ የሚያደርገው ሙከራ ጃዋር ፊሽካ እንዲነፋ ሲመድበው  አደጋ ላይ መውደቁን ከተረዳ በኃላ ነው።የፈድራል የደኅንነት መስርያ ቤት ድምፁን አጥፍቶ እያንዳንዱን የጃዋር እንቅስቃሴ ብቻ ሳይሆን  ኦዴፓ ውስጥ ያሉትን ፅንፈኛ አካሎች የመለየት ሥራ አልሰራም ብሎ መገመት አይቻልም።

የፅንፍ ኃይሎች ካሰቡት ጊዜ በፊት ለምን ወደ ነውጥ እንዲገቡ ተገደዱ?

ኢህአዴግ ውስጥ የነተሳው  የለውጥ ኃይል ሁሉንም መንገድ ክፍት ሲያደርግ ኡጋዴን እንገነጥላለን ብለው ከተነሱ ኃይሎች እስከ ኤርትራ የመሸጉት ወደ ሀገር ውስጥ ሲገቡ  ብዙ ጉድዮች እንደሚፈጠሩ ይታወቅ ነበር።በተለይ በኢትዮጵያ የፖለቲካ መስመር ውስጥ ፅንፍ የዘር እና አክራሪ እስልምና የሚያራምዱ ሁሉ የሚፈጥሩት ግጭት እንደሚኖር ይታወቃል።ይህ ሁኔታ በሂደት ይረግባል ብለው የሚያስቡ የመኖራቸውን ያህል በኃይል ብቻ መፈታት ያለባቸው የፅንፈኛ አካላት መኖራቸው ላይ ሕዝብ ስነ ልቦናዊ ዝግጅት እንዳለው የታወቀ ነው። በተለይ እነኝህ የፅንፍ ኃይሎች ከህወሓት ድጋፍ እንደሚያገኙ ከመታወቁ ጋር አሁን ከሰሞኑ የሚታየው ውጥረት ሲጠበቅ የነበረ እንጂ ድንገት ደራሽ አይደለም።

የኢትዮጵያ ፖለቲካን ወደ ባሰ የፅንፍ ጥግ ለመውሰድ የሚሯሯጡት አካሎች የመጀመርያ ስጋታቸው አንድ በሆነች ኢትዮጵያ ውስጥ የሚፈልጉትን የስልጣን መንበር እንደፈለጉ ልቆናጠጡ አለማስቻሉ ሲሆን በሌላ በኩል በመንጋ አሰባስብ ያሰባሰቡት ኃይል እየከዳቸው ሄዶ ወደ ግል ስራው  ውስጥ ከገባ እና እራሱን ከቻለ የእነርሱ ባርያ የመሆን እድሉ መቀነሱ ነው። ስለሆነም ከምርጫው በኃላ እናነሳዋለን ያሉትን ግርግር  ሳይፈልጉ ከሰሞኑ ለማንሳት ተገደዋል።ምክንያቱም እስከ አንድ ዓመት ድረስ መጠበቅ የሰበሰቡት ኃይል  ሊበተንባቸው መድረሱ አስግቷቸዋል።

መፍትሄዎቹ 

 መፍትሄው የኢትዮጵያ ሕዝብ ለመብቱ እና ለአንድነቱ የፅንፍ ኃይሎችን ጠንክሮ ካለምንም ርኅራኄ መታገል  እና የጠቅላይ ሚኒስትሩ ግልጥ ውሳኔ መስጠት የሚያስፈልግበት ጊዜ ላይ ነን። ሕዝብ የኢትዮጵያ ጉዳይ የሕልውና ጉዳይ ነው።ሕልውናው ደግሞ ከጊዜ ጋር የሚሄድ ነው።መፍዘዝ መደንዘዝ አይፈልግም። ስለሆነም በአዲስ አበባ ዙርያ ከሚደረገው የመደራጀት ሥራ ጀምሮ እስከ ገጠር የዘለቀ እንቅስቃሴ ሕዝብ ማድረግ አለበት።ይህ እንቅስቃሴ ከላይ ለመጥቀስ እንደተሞከረው ከጊዜ እና ከፍጥነት ጋር  ግን ደግሞ በከፍተኛ ግለት የፅንፈኛ ኃይልን ወደ መስመር የማስገባት ሥራ ያስፈልጋል።

በሁለተኛ ደረጃ  የስልጣን እርካቡን የያዙት ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ ካለምንም ማወላወል መውሰድ የሚገባቸው ርምጃ አለ። የመጀመርያው እርምጃ የኢትዮጵያን ፀጥታ እና አንድነት የሚገዳደሩ ማናቸውንም ኃይሎች የማንበርከክ ሥራ እንደፈድራል መንግስት መስራት አለባቸው።እነኝህ ኃይሎች ከፅንፈኛ አመለካከት ይዘው ሊገለብጧቸው ከሚያሴሩት  የኦደፓ መረብ እስከ የጀዋር ቡድን እና እንዲሁም እስከ  የህወሓት የታጠቀ ኃይል ላይ ፈጣን ምት መምታት አለባቸው።ለምሳሌ ጀዋር መሬት የመንግስት ነው በተባለባት ሀገር በአደባባይ ጦርነት ማወጁ በራሱ በሕግ የሚያስጠይቀው ነው።ስለሆነም በሕግ ጀዋርን ፍርድ ቤት ማቅረብ የዶ/ር ዓቢይ መንግስት  ካልቻለ እና በልዩ ኃይል ስም ከመከላከያ ውጭ ማንም እንዲይዝ ያልተፈቀደው ከባድ መሳርያ የታጠቀው ህወሓት የተመረጡ የመሳርያ ማከማቻ እና ካምፕ በአየር ነጥሎ እስከመመታት ድረስ ፈጣን እርምጃ መውሰድ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ይጠበቃል።ይህንን የምንለው ጠቅላይ ሚኒስትሩ የጦር ኃይሎች አዛዥ እንደመሆናቸው ኃላፊነት አለባቸው።እነኝህን ስራዎች ከሰሩ በኃላ በዓማራ እና በትግራይ መሐል የተነሳውን ችግር የመፍታት እና ልዩ ኃይል የሚባሉ አካሎች በእየክልሉ መጠናቸው እና  የሚይዙት የመሳርያ ዓይነት በሕግ መደንገግ ይቻላል።ከእዚህ ባነሰ ግን አሁን ያለው ችግር አዲስ ነፍጠኛ አካል ወደ ስልጣን የመምጣቱ ሐቅ ከፊት ለፊት የተቀመጠ አጀንዳ ነው።

ባጠቃላይ የኢትዮጵያ የፖለቲካ መድረክ እየጠራ ነው።እየጠራ ማለት ፅንፈኛው አጀንዳውም የመሸገበትም ቦታ ተለይቷል።በኢትዮጵያ አንድነንት እና ዲሞክራሲ ስር ሆኖ ሀገር ለመገንባት የተዘጋጀውም ተለይቷል።በኢትዮጵያ ሱማሌ ያለው የዑጋዴን  ታጣቂ ሳይቀር ወደ ሰላም መምጣት በራሱ የፖለቲካ መጥራቱ አካል ነው።አሁን ሕዝብ በጠነከረ መልኩ መቆም እና የጠቅላይ ሚኒስትሩ የመረረ እርምጃ የትግራይን የተመረጡ የመሳርያ ክምችት ከሕዝብ በለየ መልኩ በአየር ኃይል ከመምታት  ኦዴፓ ውስጥ ያሉ ፅንፈኞችን እና የጃዋር ግልፅ ህዝብን የማሸበር ተግባር  ለፍርድ እስከማቅረብ ድረስ መሄድ  ወሳኝ ሀገር አድን ስራዎች ናቸው።በመጨረሻም ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ በመጪው ዕሁድ  መጋቢት 1/2011 ዓም ጧት ለጋዜጠኞች በሚሰጡት መግለጫ ላይ ብዙ ነገሮች ከሰሩ በኃላ መግለጫ መስጠት አለባቸው።ከእዚህ ባለፈ በመግለጫቸው ላይ የቀደመ ተቻቻሉ መሰል ምክሮች ይዘው ከመጡ የነበራቸውን ድጋፍ በከፍተኛ ደረጃ የሚያጡበት እንዳይሆን ያሰጋል። መግለጫው ከዕርምጃ በኃላ መሆን አለበት።


ጉዳያችን GUDAYACHN
 www.gudayachn.com

No comments:

ህወሓት ሰሜን ወሎ ራያን ወርሮ የገጠር ወረዳዎችን እየዘረፈ ነው። ህዝብ ሲዘረፍ እና በአስር ሺዎች ሲፈናቀሉ የመንግስት የፖለቲካም ሆነ የወታደራዊው አመራሮች ዝምታቸው ከተጠያቂነት አያድናቸውም።

በሰሞኑ የህወሓት ወረራ ቆቦ ተፈናቅለው የገቡ የሰሜን ወሎ ተፈናቃዮች  በከፊል ፎቶ፡ ቢቢሲ ሚያዝያ 20፣2024 እኤአ ''ቅጥ አምባሩ የጠፋው'' የፕሪቶርያው ውል   ''ስኩዌር ዋን&#...