ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Tuesday, March 26, 2019

የኢትዮጵያውያን የጋራ መድረክ በኖርዌይ ''የኢትዮጵያ ወቅታዊ የፖለቲካ ሁኔታ ተስፋዎቹና ተግዳሮቶቹ '' በሚል ርዕስ ህዝባዊ ስብሰባ በኦስሎ፣ኖርዌይ ጠርቷል።

ጉዳያችን / Gudayachn
መጋቢት 18/2011 ዓም (ማርች 27/2019 ዓም )

የኢትዮጵያውያን የጋራ መድረክ በኖርዌይ መንግስት ተመዝግቦ በሕጋዊ መንገድ የሚንቀሳቀስ በዲሞክራሲያዊ ውይይቶች፣ሀሳቦች በነፃ በማንሸራሸር እና በሀገራዊ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ከየትኛውም የፖለቲካ ድርጅት ባልወገነ እና ሁሉንም የፖለቲካ እና የሲቪክ ድርጅቶች እኩል ዕድል በመስጠት የሚንቀሳቀስ ኢትዮጵያዊ መድረክ ነው።መድረኩ በመጪው ቅዳሜ መጋቢት 23/2011 ዓም (ማርች 30/2019 ዓም) ቦአስሎ በኢትዮጵያ ወቅታዊ የፖለቲካ ሁኔታ ተስፋዎቹና ተግዳሮቶቹ በሚል ርዕስ በጠራው ሕዝባዊ ስብሰባ በርካታ የኦስሎ እና አካባቢዋ ነዋሪዎች እንደሚገኙ ይጠበቃል።

የቅዳሜው ውይይት ባብዛኛው ለሚታድሙ ኢትዮጵያውያን በፖለቲካው እድሎች እና ተግዳሮቶች ዙርያ እና መወሰድ በሚገባቸው እርምጃዎች ዙርያ ሃሳብ እንዲሰጡ እድሉን የሚያመቻች እንደሚሆን ለማወቅ ተችሏል። በስብሰባው ላይ ለመገኘት ዝርዝር መረጃውን እና የጋራ መድረኩን በተመለከተ ምንነት የሚያሳይ አጭር የቪድዮ ቃለ መጠይቅ ከስር ይመልከቱ።
አዘጋጅ = የኢትዮጵያውያን የጋራ መድረክ በኖርዌይ
የውይይቱ ርዕስ : - የኢትዮጵያ ወቅታዊ የፖለቲካ ሁኔታ ተስፋዎቹና ተግዳሮቶቹ
የውይይቱ ቀን = ማርች 30/2019
ሰዓት =14 ሰዓት ጀምሮ (ሰዓት ይከበራል)
የስብሰባው ቦታ= Veterinærhøgskole
Ullevålsveien 72,0454,Oslo
(የዘንድሮው የዓድዋ በዓል ያቀበርንበት አዳራሽ)
ሁላችሁም ተጋብዛችኃል!
የኢትዮጵያውያን የጋራ መድረክ በኖርዌይ
===================================
የኢትዮጵያውያን የጋራ መድረክ በኖርዌይ ዓላማው፣ተግባሩ እና አጭር ክንውኖች ዙርያ በመስከረም/2009 ዓም የተደረገ አጭር ቃለ መጠይቅ


Attachments area


ጉዳያችን GUDAYACHN
 www.gudayachn.com

No comments: